የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ከተማዋ ያሏትን ፀጋዎች በአግባቡ በማልማት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ይጠናከራሉ

Jun 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባ ምንጭ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦አርባምንጭ ከተማ ያሏትን ፀጋዎች በአግባቡ በማልማት ማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማዋ አስተዳደር አስታወቀ።

መንግስት የከተሞችን ገጽታ በመለወጥ ለነዋሪዎች ምቹ ከማድረግ ባለፈ የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ እንዲሆኑ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።

በዚህም በሀገሪቱ በሚገኙ ከተሞች በስፋት እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር፣ የወንዝና የሀይቅ ዳርቻ የልማት ስራዎች ገፅታን ከመቀየር ያለፈ ግብን ይዘው እየተከናወኑ ነው።

ይህም ከተሞቹን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹ በማድረግ ፈጣን ዕድገት እንዲያስመዘግቡ እያገዘ ሲሆን የአርባ ምንጭ ከተማም በልማት ስራዎቹ በፈጣን ዕድገት ውስጥ ከሚገኙ ከተሞች አንዷ እየሆነች ነው።

የከተማዋ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን መንዛ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ከተማዋ ያሏትን ፀጋዎች በአግባቡ በማልማት ማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ይጠናከራሉ።

የለውጡ መንግስት ከተሞችን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ በዘረጋው ትልም የከተማዋ ፀጋዎች ተገልጠው ወደ ሀብት እየተቀየሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት የእግረኞች፣ የብስክሌት፣ የአረንጓዴ ልማት፣ የህዝብ መዝናኛ፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎችን ያካተተ 20 ኪሎ ሜትር የተቀናጀ የኮሪደር ልማት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ከእነዚህም በተለየ ስያሜ እየተገነቡ ያሉ የደረጃ መንገዶችን ጨምሮ የኩልፎ ወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች የከተማዋን ፈጣን ዕድገት ማሳያዎች ናቸው ብለዋል።

በከተማው በመንግስትና በህዝቡ ተሳትፎ የተገነቡ የህክምና ተቋማትና ደረጃውን የጠበቀ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መኖሩን ጠቅሰው የከተማዋን ዕድገት ለማፋጠን እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

የከተማዋ ነዋሪዎች በበኩላቸው፤ እየተከናወኑ የሚገኙ አዳዲስ የልማት ፕሮጀክቶች የከተማዋን ዕድገት እያፋጠኑ መሆኑን መስክረዋል።

አቶ ሙሴ ጉማራ የተባሉ የከተማዋ ነዋሪ እንደገለፁት፤ በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉት የኮሪደር፣ የወንዝ ዳርቻና የስታዲየም ግንባታዎችና ሌሎች መሰረተ ልማቶች በከተማዋ ፈጣን ዕድገት እንዲመጣ እያደረጉ ነው ብለዋል።

የመንገድ እና የመብራት መሠረተ ልማቶች እንዲሁም የቤቶች፣ የጤና እና የትምህርት ተቋማት ዘመኑን በሚመጥን መልኩ በመገንባታቸው የከተማዋ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት እየተረጋገጠ ይገኛል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው

አሶሳ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው ሲሉ የቤ...

Jun 24, 2026

አዲስ አበባ በኮሪደርና በወንዝ ዳርቻ ልማት እንደ አዲስ ነው የተወለደችው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ በአጭር ጊዜ የተገነቡ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች ከተማዋን አዘምነዋታል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸ...

Jun 23, 2026

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026