የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ የዲጂታል እመርታ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ዕድገትን በማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው

Jun 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ የዲጂታል ዘርፍ እመርታ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ዕድገትን በማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬተሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ገለጹ።

በኢትዮጵያ እና እንግሊዝ መካከል ያለው ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማሳደግ የተዘጋጀው የኢትዮ-እንግሊዝ የንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም 2026 በለንደን ከተማ ተካሂዷል።


የኢትዮ-እንግሊዝ የንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም ጎን ለጎንም በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂና ዲጂታላይዜሽን ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት ተካሄዷል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬተሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም በዚሁ መድረክ፤ በሀገራዊ ለውጡ ማግስት ኢትዮጵያ ስኬታማ የቴክኖሎጂና የኢኮኖሚ ማሻሻያ ማድረጓን አስረድተዋል።

የግብርና፣ኢንዱስትሪ፣ ማዕድንና ቱሪዝም ዘርፍ የሚያስመዘግቡትን እመርታዊ ዕድገትም ዲጂታል ቴክኖሎጂ እያሳለጠ እንደሚገኝ አንስተዋል።

የኢትዮጵያ አምስቱ የብዝኅ ኢኮኖሚ ዕድገት መሰሶዎችም በዲጂታል መሰረተ ልማት ታግዞ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል።

የዲጂታል ዘርፍ የኢትዮጵያ ብዝኅ ኢኮኖሚ መሰሶ አካል መደረጉም በአጠቃላይ የኢኮኖሚ ሥርዓት ላይ ሥር ነቀል ለውጥ እንዲመጣ ማድረጉን አስረድተዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሚመራው የዲጂታላይዜሽን ሂደት ዋና ስትራቴጂ ደረጃዎችን ወደ ላቀ ምዕራፍ ማሸጋገር እንዳስቻለም ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ዘርፍ የበለፀጉ ሀገራት ያለፉበትን ልምድና ተሞክሮ በመውሰድና ከነባራዊ አውድ ጋር በማጣጣም በወሳኝ የሽግግር ሂደት ላይ እያለፈች መሆኗን ገልጸዋል።

የዲጂታል ዘርፍ እመርታም ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ዕድገትን በማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አስረድተዋል።

በፓናል ውይይቱ አወያይ የነበሩት የምጣኔ ሃብት ባለሙያ ዘመዴነህ ንጋቱ እንዳሉት፤ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በአስደናቂ የዕድገት ምዕራፍ እያለፈች ነው።

በዚህም በመሰረተ ልማትና በዲጂታል ዘርፍ የተመዘገበው እመርታዊ ውጤትም ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ አስቻይ የትራንስፎርሜሽን ምኅዳር መፍጠሩን አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው

አሶሳ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው ሲሉ የቤ...

Jun 24, 2026

አዲስ አበባ በኮሪደርና በወንዝ ዳርቻ ልማት እንደ አዲስ ነው የተወለደችው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ በአጭር ጊዜ የተገነቡ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች ከተማዋን አዘምነዋታል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸ...

Jun 23, 2026

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026