የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ የዲጂታል እመርታ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ዕድገትን በማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው

Jun 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ የዲጂታል ዘርፍ እመርታ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ዕድገትን በማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬተሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ገለጹ።

በኢትዮጵያ እና እንግሊዝ መካከል ያለው ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማሳደግ የተዘጋጀው የኢትዮ-እንግሊዝ የንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም 2026 በለንደን ከተማ ተካሂዷል።


የኢትዮ-እንግሊዝ የንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም ጎን ለጎንም በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂና ዲጂታላይዜሽን ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት ተካሄዷል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬተሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም በዚሁ መድረክ፤ በሀገራዊ ለውጡ ማግስት ኢትዮጵያ ስኬታማ የቴክኖሎጂና የኢኮኖሚ ማሻሻያ ማድረጓን አስረድተዋል።

የግብርና፣ኢንዱስትሪ፣ ማዕድንና ቱሪዝም ዘርፍ የሚያስመዘግቡትን እመርታዊ ዕድገትም ዲጂታል ቴክኖሎጂ እያሳለጠ እንደሚገኝ አንስተዋል።

የኢትዮጵያ አምስቱ የብዝኅ ኢኮኖሚ ዕድገት መሰሶዎችም በዲጂታል መሰረተ ልማት ታግዞ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል።

የዲጂታል ዘርፍ የኢትዮጵያ ብዝኅ ኢኮኖሚ መሰሶ አካል መደረጉም በአጠቃላይ የኢኮኖሚ ሥርዓት ላይ ሥር ነቀል ለውጥ እንዲመጣ ማድረጉን አስረድተዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሚመራው የዲጂታላይዜሽን ሂደት ዋና ስትራቴጂ ደረጃዎችን ወደ ላቀ ምዕራፍ ማሸጋገር እንዳስቻለም ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ዘርፍ የበለፀጉ ሀገራት ያለፉበትን ልምድና ተሞክሮ በመውሰድና ከነባራዊ አውድ ጋር በማጣጣም በወሳኝ የሽግግር ሂደት ላይ እያለፈች መሆኗን ገልጸዋል።

የዲጂታል ዘርፍ እመርታም ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ዕድገትን በማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አስረድተዋል።

በፓናል ውይይቱ አወያይ የነበሩት የምጣኔ ሃብት ባለሙያ ዘመዴነህ ንጋቱ እንዳሉት፤ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በአስደናቂ የዕድገት ምዕራፍ እያለፈች ነው።

በዚህም በመሰረተ ልማትና በዲጂታል ዘርፍ የተመዘገበው እመርታዊ ውጤትም ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ አስቻይ የትራንስፎርሜሽን ምኅዳር መፍጠሩን አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026