የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በበጀት ዓመቱ 11 ወራት ለውጭ ገበያ ከቀረቡ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች 117 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል

Jun 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):- በበጀት ዓመቱ 11 ወራት ለውጭ ገበያ ከቀረቡ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች 117 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አስራት ጤራ (ዶ/ር) አስታወቁ፡፡

ኢትዮጵያ የተለያዩ የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦን በማቀነባበር ለውጭ ገበያ በማቅረብ የውጭ ምንዛሪ ገቢ ታገኛለች፡፡

የኢትዮጵያ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አስራት ጤራ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ካላት እምቅ የእንስሳት ሀብት ተገቢውን የውጭ ምንዛሪ ገቢ እንድታገኝ የእንስሳትን ምርታማነት የሚያሳድጉ አሰራሮች ተጠናክረው ይቀጥላሉ፡፡

ኢንስቲትዩቱ የእንስሳት ዝርያዎችን ለማሻሻል አዳዲስ የፈሳሽ ናይትሮጅን ማምረቻ ማዕከላትን እያሰፋና ነባሮችን እያዘመነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በዚህም በበጀት ዓመቱ 11 ወራት ለውጭ ገበያ ካቀረባቸው የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች 117 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል፤ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የስድስት ሚሊዮን ዶላር ብልጫ አለው ብለዋል፡፡

ለውጭ ገበያ ከቀረቡ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች መካከል የበግና ፍየል ስጋ እንዲሁም የእርድ ተረፈ ምርቶች ቀዳሚዎች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የሥጋ ምርቶቹ በብዛት ወደ ውጭ ከተላኩባቸው ሀገራት መካከል የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ ሳውዲ አረቢያ፣ ኳታር መሆናቸውን ገልጸው፤ ወደ አፍሪካ ሀገራትም ይቀርባሉ ብለዋል፡፡

በአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል የእንስሳት ጤና እና ሥነ ተዋልዶ ተመራማሪ ዶክተር ቸኮል ደምስ፤ የእንስሳት ምርታማነትን ለማሳደግ በዘርፉ ለተሰማሩ ዜጎች የእንስሳት እርባታ ሳይንስ ላይ በቂ ግንዛቤ እንደሚሰጡ ገልጸዋል፡፡

ማዕከሉ የተሻሻሉ የበግና የዳልጋ ከብት ኮርማዎች ተገቢውን እንክብካቤ አግኝተው እንዲያድጉ ለማድረግ በምርምር የተደገፈ እገዛ ያደርጋል ብለዋል፡፡

በአርባ ምንጭ ግብርና ምርምር ማዕከል የእንስሳት ጤና ማሻሻያ ተመራማሪ ዶክተር ናሆም በላይ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የእንስሳት ሀብት ልማትን የሚያሳድግ ፍሬያማ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል፡፡

በቀጣይም በዘርፉ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የዘርፉ ባለሙያዎች ልምዳቸውን ለእንስሳት ሀብት ልማት ማዋል እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው

አሶሳ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው ሲሉ የቤ...

Jun 24, 2026

አዲስ አበባ በኮሪደርና በወንዝ ዳርቻ ልማት እንደ አዲስ ነው የተወለደችው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ በአጭር ጊዜ የተገነቡ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች ከተማዋን አዘምነዋታል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸ...

Jun 23, 2026

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026