🔇Unmute
ዲላ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ በከተማው የተመዘገቡ ዘርፈ ብዙ ለውጦች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላችንን እንወጣለንሲሉ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የዲላ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው መሰረት በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲ አብላጫ የምክር ቤት ወንበር በማግኘት መንግሥት ለመመስረት የሚያስችለውን ድምጽ አግኝቷል።
ለኢዜአ አስተያየታቸው የሰጡ የዲላ ከተማ ነዋሪዎች በለውጡ መንግሥት በከተማው የተመዘገቡ ዘርፈ ብዙ ለውጦች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላችንን እንወጣለን ብለዋል፡፡
ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል መምህር ዮናስ ታደለ እንደተናገሩት፤ በከተሞች መሰረተ ልማትና በኮሪደር ልማት የተከናወኑ ተግባራት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው ብለዋል።
እንዲሁም ህብረተሰቡን በማስተባበር የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የተደረጉ ጥረቶች ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት የሚደረገውን ጉዞ የሚያግዙ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በከተማው የተመዘገበው ዘርፈ ብዙ ለውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በምርጫ ያሸነፈው ብልጽግና ፓርቲ ከሚመሰርተው መንግሥት ጎን በመሰለፍ የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ነጻ፣ ገለልተኛና አሳታፊ በሆነ ምርጫ አሸናፊው ፓርቲ መታወቁ የዲሞክራሲ ባህል እየጎለበተ መምጣቱን የሚያመላክት መሆኑን ያነሱት ደግሞ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ተስፋነሽ ኢሳያስ ናቸው።
በተለይ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል፡፡
በከተማው የታየው ለውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከአሸናፊ ፓርቲው ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።
በዲላ ዩኒቨርሲቲ የታሪክና ቅርስ አስተዳደር መምህርና ተመራማሪ ሰረቀብርሃን ለገሰ በበኩላቸው፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከዝግጅት እስከ ውጤት ገለልተኝነትና አሳታፊነት በተጨባጭ የተረጋገጠበት ነው ብለዋል።
በዴሞክራሲያዊ መንገድ ወደ ስልጣን የመጣ መንግሥት ለህዝብ የልማት ጥያቄ ምላሽ ከመስጠት አንጻር የተሻለ መሆኑን አንስተው አዲሱ መንግሥት የልማት ውጥኑን ከዳር እንዲያደርስ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ተናግረዋል።
ባሕር ዳር፤ ሰኔ 19/2018(ኢዜአ)፡- በተቋማት እየተካሄደ የሚገኘውን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በላቀ የአመራር ጥበብ በመፈፀም የመልካም አስ...
Jun 27, 2026
አሶሳ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው ሲሉ የቤ...
Jun 24, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ በአጭር ጊዜ የተገነቡ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች ከተማዋን አዘምነዋታል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸ...
Jun 23, 2026
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026