የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በላቀ የአመራር ጥበብ ለመፈፀም በትኩረት እየተሰራ ነው- አቶ አረጋ ከበደ

Jun 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባሕር ዳር፤ ሰኔ 19/2018(ኢዜአ)፡- በተቋማት እየተካሄደ የሚገኘውን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በላቀ የአመራር ጥበብ በመፈፀም የመልካም አስተዳደር ችግርን ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ገለፁ።

በአማራ ክልል በመጀመሪያው ዙር ወደ መንግሥት አገልግሎት እና አሥተዳደር ሪፎርም የሚገቡ ተቋማትን የቅድመ ዝግጅት ሁኔታ በተመለከተ በባሕር ዳር ከተማ እየተገመገመ ነው።


ርእሰ መስተዳድሩ አቶ አረጋ ከበደ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ መንግስት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርምን በመቅረጽ የክልሉ ህዝብ የሚያነሳውን የመልካም አስተዳደር ችግር ለመቅረፍ እየሰራ ነው፡፡

በዚህም ለህዝቡ ፈጣን፣ ፍትሃዊና እርካታን የፈጠረ አገልግሎት ለመስጠት በቁርጠኝነት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ከዚህ ውስጥም በከተሞች መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግና በተቋማት የመንግስት አገልግሎት አስተዳደር ሪፎርምን በመተግበር ውጤታማ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በምክትል ርእሰ መስተዳድር ማእረግ የከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የሪፎርሙ ስትሪንግ ኮሚቴ ሰብሳቢ አህመዲን መሃመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው ሪፎርሙ የተቀናጀ መዋቅር፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራርና ቁርጠኛ አመራርን የሚጠይቅ ነው ብለዋል።

በአሁኑ ወቅትም ሪፎርሙን በክልል ደረጃ በተሟላ መልኩ በመተግበር ወደ ታች ለማውረድ እየተሰራ እንደሚገኝም ነው ያመለከቱት።

የዛሬው መድረክ ዋና ዓላማም ቀድመው ሪፎርሙን ተግባራዊ ያደረጉ ተቋማት አተገባበር ያለበትን ሁኔታ በመገምገም በቀጣይ የላቀ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ያለመ ነው ብለዋል።

የአማራ ክልል የሲቪል ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ባንችአምላክ ገብረማርያም እንደገለጹት፤ ባለፉት ሶስት ወራት በስምንት ተቋማት የተጀመረውን የሪፎርም ትግበራን ለማስፋት እየተሰራ ነው።

ተቋማቱ በዝግጅት ምእራፍ ስትራቴጂ በመቅረጽ፣ ማስፈጸሚያ መመሪያ በማዘጋጀትና የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት መስክ ያከናወኑት ተግባር አበረታች መሆኑን ገልጸዋል።

ይህም ከሀምሌ ወር 2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሪፎርም ትግበራው ለሚገቡ ተጨማሪ ዘጠኝ ተቋማት ልምድና ተሞክሮ ለማስተላለፍ እንደሚያስችል አስገንዝበዋል።

በመጀመሪያው ምእራፍ የሪፎርም ትግበራ ግብርና ፣ ጤና ፣ ትምህርት፣ ስራና ክህሎት፣ ሲቪል ሰርቪስ ፣ ገንዘብ ፣ ገቢዎችና ፕላን ልማት ቢሮዎች መካተታቸው የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በላቀ የአመራር ጥበብ ለመፈፀም በትኩረት እየተሰራ ነው- አቶ አረጋ ከበደ

ባሕር ዳር፤ ሰኔ 19/2018(ኢዜአ)፡- በተቋማት እየተካሄደ የሚገኘውን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በላቀ የአመራር ጥበብ በመፈፀም የመልካም አስ...

Jun 27, 2026

ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው

አሶሳ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው ሲሉ የቤ...

Jun 24, 2026

አዲስ አበባ በኮሪደርና በወንዝ ዳርቻ ልማት እንደ አዲስ ነው የተወለደችው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ በአጭር ጊዜ የተገነቡ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች ከተማዋን አዘምነዋታል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸ...

Jun 23, 2026

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026