የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በላቀ የአመራር ጥበብ ለመፈፀም በትኩረት እየተሰራ ነው- አቶ አረጋ ከበደ

Jun 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባሕር ዳር፤ ሰኔ 19/2018(ኢዜአ)፡- በተቋማት እየተካሄደ የሚገኘውን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በላቀ የአመራር ጥበብ በመፈፀም የመልካም አስተዳደር ችግርን ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ገለፁ።

በአማራ ክልል በመጀመሪያው ዙር ወደ መንግሥት አገልግሎት እና አሥተዳደር ሪፎርም የሚገቡ ተቋማትን የቅድመ ዝግጅት ሁኔታ በተመለከተ በባሕር ዳር ከተማ እየተገመገመ ነው።


ርእሰ መስተዳድሩ አቶ አረጋ ከበደ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ መንግስት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርምን በመቅረጽ የክልሉ ህዝብ የሚያነሳውን የመልካም አስተዳደር ችግር ለመቅረፍ እየሰራ ነው፡፡

በዚህም ለህዝቡ ፈጣን፣ ፍትሃዊና እርካታን የፈጠረ አገልግሎት ለመስጠት በቁርጠኝነት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ከዚህ ውስጥም በከተሞች መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግና በተቋማት የመንግስት አገልግሎት አስተዳደር ሪፎርምን በመተግበር ውጤታማ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በምክትል ርእሰ መስተዳድር ማእረግ የከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የሪፎርሙ ስትሪንግ ኮሚቴ ሰብሳቢ አህመዲን መሃመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው ሪፎርሙ የተቀናጀ መዋቅር፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራርና ቁርጠኛ አመራርን የሚጠይቅ ነው ብለዋል።

በአሁኑ ወቅትም ሪፎርሙን በክልል ደረጃ በተሟላ መልኩ በመተግበር ወደ ታች ለማውረድ እየተሰራ እንደሚገኝም ነው ያመለከቱት።

የዛሬው መድረክ ዋና ዓላማም ቀድመው ሪፎርሙን ተግባራዊ ያደረጉ ተቋማት አተገባበር ያለበትን ሁኔታ በመገምገም በቀጣይ የላቀ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ያለመ ነው ብለዋል።

የአማራ ክልል የሲቪል ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ባንችአምላክ ገብረማርያም እንደገለጹት፤ ባለፉት ሶስት ወራት በስምንት ተቋማት የተጀመረውን የሪፎርም ትግበራን ለማስፋት እየተሰራ ነው።

ተቋማቱ በዝግጅት ምእራፍ ስትራቴጂ በመቅረጽ፣ ማስፈጸሚያ መመሪያ በማዘጋጀትና የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት መስክ ያከናወኑት ተግባር አበረታች መሆኑን ገልጸዋል።

ይህም ከሀምሌ ወር 2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሪፎርም ትግበራው ለሚገቡ ተጨማሪ ዘጠኝ ተቋማት ልምድና ተሞክሮ ለማስተላለፍ እንደሚያስችል አስገንዝበዋል።

በመጀመሪያው ምእራፍ የሪፎርም ትግበራ ግብርና ፣ ጤና ፣ ትምህርት፣ ስራና ክህሎት፣ ሲቪል ሰርቪስ ፣ ገንዘብ ፣ ገቢዎችና ፕላን ልማት ቢሮዎች መካተታቸው የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026