የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ቢሮው ተግባራዊ ያደረጋቸው በቴክኖሎጂ የተደገፉ አዳዲስ አሠራሮች የአገልግሎት አሰጣጡን ከማዘመን ባለፈ የከተማዋን የገቢ አቅም አሳድጓል

Jun 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ተግባራዊ ያደረጋቸው በቴክኖሎጂ የተደገፉ አዳዲስ አሠራሮች የአገልግሎት አሰጣጡን ከማዘመን ባለፈ የከተማዋን የገቢ አቅም ማሳደጉን አስታወቀ፡፡

ቢሮው ቀደም ሲል ግብር ከፋዮች በአካል በመቅረብና የወረቀት ሰነዶችን በመያዝ ያገኙት የነበረውን አገልግሎት ሙሉ ለሙሉ ወደ ኦንላይን ሥርዓት ማሸጋገር ችሏል።

የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ የሞደርናይዜሽን ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መሃመድ አብዱረህማን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ቢሮው ባለፉት ሁለት ዓመታት በርካታ የሪፎርም ሥራዎችን አከናውኗል።

ግብር ከፋዮች በአካል ሳይመጡ በኢሜል እና በተዘረጋው የኦንላይን ሊንክ አገልግሎቱን ማግኘት እንዲችሉ ከፌደራል ገቢዎች ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት የተቀናጀ የልማት ሥርዓት ተዘርግቶ ወደ ተግባር መገባቱን ጠቁመዋል።

ይህ አዲስ አሠራር ግብር ከፋዮች ባሉበት ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበት ምኅዳር የፈጠረ ሲሆን፣ የባለቤትነት ስም ዝውውርን ጨምሮ የተለያዩ የሕግ ተገዥነት አገልግሎቶችን ያካተተ መሆኑን አስረድተዋል።

ቢሮው በራሱ አቅም ያለማውን የዕዳ ክትትል ሥርዓት ወደ ተግባር በማስገባቱ በ17ቱም ቅርንጫፎች የሚወሰኑ የዕዳ ውሳኔዎችን በቅርበት ለመከታተልና የሚሰበሰበውን ገቢ ወደ ገንዘብ በመለወጥ ረገድ ከፍተኛ አፈጻጸም ተመዝግቧል።

የክሊራንስ አሰጣጥ ሂደቱን ይበልጥ ግልጽ፣ ቀልጣፋና እምነት የሚጣልበት ለማድረግ ባርኮድ ያለው አዲስ የኦንላይን አሠራር ተግባራዊ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡

የተዘረጉት የዲጂታል አገልግሎቶች ግብር ከፋዮች ባሉበት ሆነው ግብራቸውን እንዲያሳውቁና እንዲከፍሉ በማድረጉ፣ በየወሩ መጨረሻ ላይ በቅርንጫፍ ቢሮዎች ይታይ የነበረውን ከፍተኛ መጨናነቅና የረጅም ጊዜ ጥበቃ ማስቀረት መቻሉንም ጠቁመዋል፡፡

ቢሮው በቀጣዩ በጀት ዓመትም የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮችን የሚያስተናግደውን የኢቲ ታክስ (eTax) ሥርዓት ሙሉ ለሙሉ ወደ ዲጂታል በማሸጋገር፣ ግብር ከፋዮች ባሉበት ሆነው አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችሉ ማሻሻያዎችን እንደሚተገብር ገልጸዋል።

በከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ የኤሌክትሮኒክስ ታክስ ግብይት ድጋፍና ክትትል የሥራ ሂደት ተወካይ አቶ ሰይድ መሃመድ፤ ለግብር ከፋዮች ስለ አገልግሎቱ አጠቃቀም በቂ ስልጠናና ተከታታይ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።


የቅርንጫፉ የኤሌክትሮኒክስ ታክስ ክፍያ አሰባሰብና ክትትል ቡድን አስተባባሪ ተወካይ አቶ ኢድሪስ መሃመድ በበኩላቸው፣ አዲሱ የዲጂታል ሥርዓት ተቋማዊ አፈጻጸምን ከማሳደግና ሥራዎችን ከማቅለል አንጻር ሰፊ ፋይዳ እንዳለው አብራርተዋል።


የቅርንጫፉ ተገልጋዮችም በአዲሱ አሠራር መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡

አቶ ታምራት አብራሃም በሰጡት አስተያየት አዲሱ የኦንላይን ሥርዓት ረጅም ሰልፍን ያስቀረና ተገልጋዩ በቤቱ ሆኖ ሁሉንም አገልግሎት ማግኘት እንዲችል ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አዲሱ አሠራር በሥራቸውና በድርጅታቸው ላይ ዘርፈ-ብዙ ጥቅሞችን እንዳስገኘላቸው የገለጹት ደግሞ አቶ ሙልጌታ ተሻለ ናቸው፡፡

አቶ እስጢፋኖስ ብርሃኔ በበኩላቸው የዲጂታል አሠራሩ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ በማስቻል ይደርስባቸው የነበረውን ከፍተኛ እንግልት ሙሉ በሙሉ ማስቀረቱን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በላቀ የአመራር ጥበብ ለመፈፀም በትኩረት እየተሰራ ነው- አቶ አረጋ ከበደ

ባሕር ዳር፤ ሰኔ 19/2018(ኢዜአ)፡- በተቋማት እየተካሄደ የሚገኘውን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በላቀ የአመራር ጥበብ በመፈፀም የመልካም አስ...

Jun 27, 2026

ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው

አሶሳ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው ሲሉ የቤ...

Jun 24, 2026

አዲስ አበባ በኮሪደርና በወንዝ ዳርቻ ልማት እንደ አዲስ ነው የተወለደችው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ በአጭር ጊዜ የተገነቡ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች ከተማዋን አዘምነዋታል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸ...

Jun 23, 2026

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026