የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ 

Jun 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

ስምምነቱ በረጅም ጊዜ የሚከፈል የብድር ስምምነት ሲሆን ለሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የልማት ሥራዎች ማስፈጸሚያ የሚውል መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ገልጸዋል።

የብድር ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ እና በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ሴም ፋብሪዚ ተፈራርመውታል።


የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ይህ የብድር ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጠንካራ አጋርነት የሚያሳይና የረጅም ጊዜ ታሪካዊ ግንኙነታቸውን ይበልጥ የሚያጠናክር ነው።


ስምምነቱ ቀደም ሲል በሁለቱ ሀገራት መካከል የተደረሱት የትብብር ማዕቀፎች አካል መሆኑንም ጠቁመዋል።

የገንዘብ ድጋፉ ኢትዮጵያ የጀመረቻቸውን ሀገራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎችና የልማት ግቦችን ለማሳካት አስተዋፅዖ እንደሚኖረው አስረድተዋል።


ኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ተግባራዊ በማድረግ ሁለተኛውን ምዕራፍ በስኬት ማጠናቀቋን ገልጸዋል።

ይህንኑ ተከትሎ የዓለም ባንክ ለሶስተኛው ምዕራፍ የሪፎርም ትግበራ የሚውል የበጀት ድጋፍ ማፅደቁንም አስታውሰዋል።

የጣሊያን መንግሥት ለኢትዮጵያ የልማት ጥረቶችና የኢኮኖሚ ማሻሻያ ለሚያደርገው የገንዘብ ድጋፍና ቀጣይነት ላለው አጋርነት ምስጋና አቅርበዋል።

አምባሳደር ሴም ፋብሪዚ በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ የ10 ዓመት መሪ የልማት ዕቅድ እና የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ሀገሪቱን በትክክለኛ የዕድገት አቅጣጫ እየመራት መሆኑን ገልጸዋል።


መንግስታቸውም ይህንን ሂደት በቁርጠኝነት እንደሚደግፍ አረጋግጠዋል።

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተግባር ለማገዝ የሚያስችል የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ከዓለም ባንክ መርሆዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ መፈጸሙን አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በረጅም ጊዜ የሚከፈል የብድር ስምምነ...

Jun 30, 2026

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በላቀ የአመራር ጥበብ ለመፈፀም በትኩረት እየተሰራ ነው- አቶ አረጋ ከበደ

ባሕር ዳር፤ ሰኔ 19/2018(ኢዜአ)፡- በተቋማት እየተካሄደ የሚገኘውን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በላቀ የአመራር ጥበብ በመፈፀም የመልካም አስ...

Jun 27, 2026

ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው

አሶሳ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው ሲሉ የቤ...

Jun 24, 2026

አዲስ አበባ በኮሪደርና በወንዝ ዳርቻ ልማት እንደ አዲስ ነው የተወለደችው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ በአጭር ጊዜ የተገነቡ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች ከተማዋን አዘምነዋታል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸ...

Jun 23, 2026