የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው 

Jul 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለፁ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፣ የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የሀብት ማሰባሰቢያ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።


የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በዚህ ወቅት፤ የሲዳማ ክልል የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ባለሀብቶች ወደ ሀዋሳ በመምጣት እውቀትና ሀብታቸውን ተጠቅመው በኢንቨስትመንት እንዲሰማሩ ርዕሰ መስተዳድሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ሀዋሳ መተላለፊያና ማረፊያ ከተማ በመሆኗ ባለሃብቶች በአካባቢው ያለውን ዕድል እንዲጠቀሙ ጠይቀዋል።

ሀዋሳን በጋራ ለመገንባት የቀረበውን ጥሪ ተቀብለው በቁርጠኝነት ለሰሩና የበኩላቸውን ሚና ለተወጡም ምስጋና አቅርበዋል።

ሀዋሳ የደቡብ ፈርጥ፣ የሰላም ደሴት፣ ባላት ውብ ተፈጥሮ ምድረ ገነት የተባለች፣ እንዲሁም የህዝቡ እንግዳ ተቀባይነት የፍቅር ቤት ያስባላት ከተማ መሆኗን አንስተዋል።

ሀዋሳን ለኑሮ፣ ለመዝናኛ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት የተመቸች ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው፣ የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የሀብት ማሰባሰቢያ መድረክ የፕሮጀክት መገንቢያ ብቻ ሳይሆን፣ የነገንና አዲሱን ምዕራፍ በጋራ ለመገንባት መሆኑን ገልጸዋል።


ሀዋሳ በተፈጥሮ የታደለች ናት ያሉት ከንቲባው፤ ከተማዋን አልምቶ ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ ተናግረዋል።

የሀዋሳ ሐይቅ የቱሪዝም ምንጭና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን አንስተው፤ የሐይቁን ዳርቻ ማልማት የከተማዋን ገጽታና ተስፋ የሚቀይር ታሪካዊ ስራ መሆኑንም ገልጸዋል።

ሀዋሳን ለኑሮ፣ ለኢንቨስትመንት፣ ለቱሪዝም ምቹ እንዲሁም ከተማዋን የአፍሪካ የቱሪዝምና የኮንፍረንስ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የፍቅር ሐይቅ፣ አሞራ ገደልና ዓሳ ገበያን ለነዋሪዎቿና ለቱሪስቶች ምቹ ለማድረግ መታቀዱንም ተናግረዋል።

ከተማዋን በዘመናዊ መንገድ ለመገንባት ለተወጠነው ፕሮጀክት ከሦስት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በላይ በጀት እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ ከዚህ መካከል ሁለት ቢሊዮን ብር ከከተማ አስተዳደሩ፣ አንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብሩን በገቢ ማሰባሰቢያ ለማግኘት መታቀዱን አስረድተዋል።

ባለፉት ሁለት ወራት በቀረበው ጥሪ መሰረት በመጀመሪያው ዙር የሀብት ማሰባሰቢያ ድጋፍ ሲደረግ መቆየቱን ጠቅሰው፤ የዛሬው መድረክም የመጀመሪያ ዙር የሀብት ማሰባሰቢያ ማጠናቀቂያ መሆኑን ተናግረዋል።

የሀዋሳ ሐይቅን ለማልማት የከተማዋ ነዋሪዎች፣ ባለሃብቶችና ባለድርሻ አካላት ድጋፍ ማድረጋቸውንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስ...

Jul 7, 2026

የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ጥገናን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው

ኮምቦልቻ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፡- የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Jul 1, 2026

ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በረጅም ጊዜ የሚከፈል የብድር ስምምነ...

Jun 30, 2026

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በላቀ የአመራር ጥበብ ለመፈፀም በትኩረት እየተሰራ ነው- አቶ አረጋ ከበደ

ባሕር ዳር፤ ሰኔ 19/2018(ኢዜአ)፡- በተቋማት እየተካሄደ የሚገኘውን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በላቀ የአመራር ጥበብ በመፈፀም የመልካም አስ...

Jun 27, 2026