🔇Unmute
ጅማ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ ጅማ ዩኒቨርሲቲ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሽታን የሚቋቋሙና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያቸው የተሻሻሉ የቡና ችግኞችን ለአካባቢው ማህበረሰብ እያሰራጨ መሆኑን አስታወቀ።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ዘርፈ ብዙ የምርምር ሥራዎችን እንደሚያከናውን ጠቅሰው፣ ከእነዚህ መካከል የተሻሻሉ የቡና ችግኞችን በማዘጋጀት ለሕብረተሰቡ ማሰራጨት አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ለዘንድሮው ክረምት በዩኒቨርሲቲው ለአረንጓዴ ዐሻራ ከተዘጋጁትና የተለያየ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ካላቸው ችግኞች በተጨማሪ፣ አንድ ሚሊየን በሽታን የሚቋቋሙ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች እንደሚገኙበት ገልጸዋል።
የቡና ችግኞቹ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ምርት መስጠት የሚችሉ በመሆናቸው፣ ከአርሶ አደሩ በተጨማሪ ቡናን ለሚያለሙ ባለሀብቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረቡ መሆናቸውን አስረድተዋል።
በተጨማሪም ከ500 ሺህ በላይ የፍራፍሬ፣ የውበት እና ሌሎች የሀገር በቀል ዕፅዋት ችግኞችን ለመትከል መታቀዱንም ጠቁመዋል።
ዩኒቨርሲቲው የፍራፍሬ ምርትን ይበልጥ ለማስፋፋትና ለሕብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በሁለት ወረዳዎች ላይ ዝግጅት እያደረገ መሆኑንም አክለዋል።
በዩኒቨርሲቲው የግብርና እና እንስሳት ሕክምና ኮሌጅ ዲን ሰለሞን ቱሉ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የቡና ምርት ሊያሳድጉ የሚችሉ የተሻሻሉ ዝርያዎች በሦስት የዩኒቨርሲቲው ካምፓሶች እየተዘጋጁ ለማኅበረሰቡ ሲሰራጩ መቆየታቸውን ጠቁመዋል።
በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርም፣ በተለይም በዩኒቨርሲቲው ግብርና እና እንስሳት ሕክምና ኮሌጅ የምርምር ተቋም አማካኝነት ይህ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቀዋል።
ዩኒቨርሲቲው የግብርና ሥራውን የሚያስፋፋው የተፈጥሮ ማዳበሪያዎችን በስፋት በመጠቀም እንደሆነ ገልጸው፣ በዘንድሮው ዓመት ብቻ 120 ቶን የተፈጥሮ ማዳበሪያ መዘጋጀቱን አክለዋል።
ከዩኒቨርሲቲው የቡና ችግኝ ከወሰዱ ባለሀብቶች መካከል አቶ ግደይ በርሄ እንደገለጹት በራሳቸው ከሚያዘጋጁት በተጨማሪ የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ከዩኒቨርሲቲው በመውሰድ እያለሙ ይገኛሉ።
የቡና ችግኙን በ350 ሄክታር መሬት ላይ በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመው በልማቱም ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠራቸውን አክለዋል።
ከዩኒቨርሲቲው የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን በመውሰድ በሰፊው እያለሙ እንደሚገኙ የተናገሩት ደግሞ ሌላኛው ተጠቃሚ አቶ ፈለቀ ሌንጮ የቡና ችግኞቹ በብዛትና በጥራት ምርት የሚሰጡ ስለሆኑ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን በተሻለ ሁኔታ እያሳደገላቸው መሆኑን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስ...
Jul 7, 2026
ኮምቦልቻ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፡- የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Jul 1, 2026
አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በረጅም ጊዜ የሚከፈል የብድር ስምምነ...
Jun 30, 2026
ባሕር ዳር፤ ሰኔ 19/2018(ኢዜአ)፡- በተቋማት እየተካሄደ የሚገኘውን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በላቀ የአመራር ጥበብ በመፈፀም የመልካም አስ...
Jun 27, 2026