🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ወርቅ በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ 5 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር የማስገኘት አቅም ፈጥሯል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ በሰጡት የወርቅ እመርታዊ ውጤቶች ማብራሪያቸው፤ ከ1984 እስከ 2011 ዓ.ም ድረስ በሃያ ሰባት ዓመታት ውስጥ በድምሩ የኢትዮጵያ ወርቅ ከወጪ ንግድ 3 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማስገኘቱን አስታውሰዋል።
በአንድ ዓመት ውስጥ ግን ከወርቅ ወጪ ንግድ 5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማገኘት የተቻለበትን አቅም መፍጠሩን አስታውቀዋል።
በአንድ ዓመት ውስጥ የተመዘገበው እመርታ የ27 ዓመታት ሥራን እንደሚበልጥ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይህ ዓይነቱ ስኬት እውነተኛ የዕድገት ማረጋገጫ መሆኑን አስምረውበታል።
በኢትዮጵያ ቁጥር ሳይሆን የሚጨበጥና የሚዳሰስ የሚታይም ዕድገት ነው እየመጣ የሚገኘው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስ...
Jul 7, 2026
ኮምቦልቻ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፡- የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Jul 1, 2026
አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በረጅም ጊዜ የሚከፈል የብድር ስምምነ...
Jun 30, 2026
ባሕር ዳር፤ ሰኔ 19/2018(ኢዜአ)፡- በተቋማት እየተካሄደ የሚገኘውን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በላቀ የአመራር ጥበብ በመፈፀም የመልካም አስ...
Jun 27, 2026