የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ንግድና ኢንቨስትመንት ፍሰትን በማሳደግ እመርታዊ ውጤት እያስገኘ ነው

Jul 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ንግድና ኢንቨስትመንት ፍሰትን በማሳደግ እመርታዊ ውጤት እያስገኘ መሆኑን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ዮሐንስ ፋንታ ገለጹ።

የኢትዮጵያ ንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ከፍተኛ የኤክስፖርትና የዲፕሎማሲ ፎረም የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የሀገራት ዲፕሎማቶች፣ የኢትዮጵያ ላኪዎች፣ አምራቾችና ባለድርሻ አካላት መተገኙበት እየተካሄደ ነው።

በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ዮሐንስ ፋንታ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ተከታታይነት ያለው ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገበች ነው ብለዋል።


ኢትዮጵያ ለጠንካራ የንግድ ኢንቨስትመንትና ለቀጣናዊ ትስስር ማዕከል ለመሆን ምቹ ሁኔታ ያላት መሆኗን ገልጸዋል።

ይህም የወጪ ንግድን ለማጠናከርና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶችን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ዲፕሎማሲ የኢኮኖሚ ግንኙነቶችንና አጋርነት የሚጠናከርበትና ዘላቂ ልማት በተግባር የሚረጋገጥበት ስትራቴጂያዊ መሣሪያ መሆኑንም አክለዋል።

በዚህም መሰረት መንግሥት ኢትዮጵያን በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ያላትን እምቅ ሀብቶች ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የማስተዋወቅ ስራውን አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ ንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ዋና ፀሀፊ ቀነኒሳ ለሚ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የፎረሙ ዋና ዓላማ የኢትዮጵያን የኤክስፖርት ምርቶች፣ አገልግሎቶችና የኢንቨስትመንት አማራጮች ለዓለም አቀፍ አጋሮች ማስተዋወቅ መሆኑን ተናግረዋል።

መንግሥት የጀመረው የሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፉ የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ ለመዳሰስና ለባለሃብቶች ለማስተዋወቅ ፎረሙ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው አስረድተዋል።

የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተዘጋጀው መድረክ የኢትዮጵያን ምርቶችና አገልግሎቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ለማስተዋወቅ ጠንካራና ይበልጥ የተቀናጀ አሰራር ለመፍጠር ያግዛል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስ...

Jul 7, 2026

የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ጥገናን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው

ኮምቦልቻ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፡- የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Jul 1, 2026

ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በረጅም ጊዜ የሚከፈል የብድር ስምምነ...

Jun 30, 2026

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በላቀ የአመራር ጥበብ ለመፈፀም በትኩረት እየተሰራ ነው- አቶ አረጋ ከበደ

ባሕር ዳር፤ ሰኔ 19/2018(ኢዜአ)፡- በተቋማት እየተካሄደ የሚገኘውን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በላቀ የአመራር ጥበብ በመፈፀም የመልካም አስ...

Jun 27, 2026