የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ንግድና ኢንቨስትመንት ፍሰትን በማሳደግ እመርታዊ ውጤት እያስገኘ ነው

Jul 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ንግድና ኢንቨስትመንት ፍሰትን በማሳደግ እመርታዊ ውጤት እያስገኘ መሆኑን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ዮሐንስ ፋንታ ገለጹ።

የኢትዮጵያ ንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ከፍተኛ የኤክስፖርትና የዲፕሎማሲ ፎረም የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የሀገራት ዲፕሎማቶች፣ የኢትዮጵያ ላኪዎች፣ አምራቾችና ባለድርሻ አካላት መተገኙበት እየተካሄደ ነው።

በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ዮሐንስ ፋንታ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ተከታታይነት ያለው ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገበች ነው ብለዋል።


ኢትዮጵያ ለጠንካራ የንግድ ኢንቨስትመንትና ለቀጣናዊ ትስስር ማዕከል ለመሆን ምቹ ሁኔታ ያላት መሆኗን ገልጸዋል።

ይህም የወጪ ንግድን ለማጠናከርና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶችን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ዲፕሎማሲ የኢኮኖሚ ግንኙነቶችንና አጋርነት የሚጠናከርበትና ዘላቂ ልማት በተግባር የሚረጋገጥበት ስትራቴጂያዊ መሣሪያ መሆኑንም አክለዋል።

በዚህም መሰረት መንግሥት ኢትዮጵያን በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ያላትን እምቅ ሀብቶች ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የማስተዋወቅ ስራውን አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ ንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ዋና ፀሀፊ ቀነኒሳ ለሚ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የፎረሙ ዋና ዓላማ የኢትዮጵያን የኤክስፖርት ምርቶች፣ አገልግሎቶችና የኢንቨስትመንት አማራጮች ለዓለም አቀፍ አጋሮች ማስተዋወቅ መሆኑን ተናግረዋል።

መንግሥት የጀመረው የሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፉ የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ ለመዳሰስና ለባለሃብቶች ለማስተዋወቅ ፎረሙ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው አስረድተዋል።

የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተዘጋጀው መድረክ የኢትዮጵያን ምርቶችና አገልግሎቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ለማስተዋወቅ ጠንካራና ይበልጥ የተቀናጀ አሰራር ለመፍጠር ያግዛል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026