የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኮሪደር ልማትና ሌሎች ፕሮጀክቶች የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና የሀገርን ገጽታ የቀየሩ ናቸው

Jul 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/ 2018 (ኢዜአ):-የኮሪደር ልማትና ሌሎች ፕሮጀክቶች የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና የሀገርን ገጽታ የቀየሩ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትናንትናው ዕለት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ የሥራ ዘመን 3ኛ ዓመት 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው፤ የኮሪደር ልማቱ ዋና ዓላማ የሕዝቡን የኑሮ ደረጃ ማሻሻል፣ ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ ማድረግና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን ማነቃቃት መሆኑን ጠቅሰዋል።

ልማቱ ከከተሞች ደረጃና ውበት፣ ከመሠረተ ልማት ትስስር፣ ከደህንነት እንዲሁም ከመብራት አገልግሎትና ከሌሎች ተያያዥ ጠቀሜታዎች አንጻር ያለውን ፋይዳም አብራርተዋል።


የኮሪደር ልማትና ሌሎች ስትራቴጂያዊ የልማት ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ገጽታ የሚቀይሩ በመሆናቸው፤ መላው ሕዝብ፣ ባለሀብቶችና ተፎካካሪ ፓርቲዎች ለሀገር ግንባታው በጋራ እንዲቆሙ ጥሪ ማቅረባቸውም ይታወቃል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በበኩላቸው፤ ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ በተከናወኑ የኮሪደርና ሌሎች የልማት ሥራዎች የዜጎችን ተጠቃሚነት ከፍ ወዳለ ደረጃ እያሸጋገሩት እንደሚገኙ ገልጸዋል።

የልማት ሥራዎቹ ለትውልዱ ትምህርት የሚሰጡና የሥራ ባህልን ለማሳደግ ምሳሌ የሚሆኑ ያሉት ነዋሪዎቹ፥ በአፍሪካም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሀገርን ገጽታ መቀየራቸውን ተናግረዋል።

ወይዘሮ ተሊሌ ኃብተማርያም ፤ የኮሪደር ልማትና ሌሎች የልማት ሥራዎች ወጣቶችና ሴቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረጋቸውን አንስተዋል።


አቶ ሙደስር ኡመር በበኩላቸው፤ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በኢትዮጵያ በተከናወኑ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ከተሞችን ንጹሕና ለነዋሪዎች ምቹ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

ትውልዱ ከዚህ ትምህርት ሊወስድ፣ በሚከናወኑ ሥራዎች በትጋት ሊሠራና ከመንግሥት ጎን በመሆን ለሀገር ግንባታ አሻራውን ሊያሳርፍ ይገባልም ብለዋል።


ሌላዋ የመዲናዋ ነዋሪ ወይዘሮ አዲስ ዓለም ምስግና በኢትዮጵያ የታየው ለውጥ በአጭር ጊዜ ውስጥ በርካታ ዕቅዶችን ማሳካት እንደሚቻል በተጨባጭ ያመላከተ መሆኑን ተናግረዋል።


የልማት ሥራዎቹ በስራ እድል ፈጠራና የኑሮ ደረጃን በማሻሻል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት አሳድገዋል ያሉት አቶ ታምራት ቶሎሳ፥ ከኢትዮጵያ ባለፈ አፍሪካውያንን ለላቀ ልማት ያነሳሱ ናቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስ...

Jul 7, 2026

የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ጥገናን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው

ኮምቦልቻ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፡- የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Jul 1, 2026

ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በረጅም ጊዜ የሚከፈል የብድር ስምምነ...

Jun 30, 2026

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በላቀ የአመራር ጥበብ ለመፈፀም በትኩረት እየተሰራ ነው- አቶ አረጋ ከበደ

ባሕር ዳር፤ ሰኔ 19/2018(ኢዜአ)፡- በተቋማት እየተካሄደ የሚገኘውን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በላቀ የአመራር ጥበብ በመፈፀም የመልካም አስ...

Jun 27, 2026