የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀልጣፋ አገልግሎት እያገኘን ነው

Jul 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሚዛን አማን፣ ሐምሌ 5/2018 (ኢዜአ)-:-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀልጣፋና ከሙስና የጸዳ አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን ተገልጋዮች ገለጹ፡፡

በክልሉ በሁለተኛ ዙር የተገነቡ አምስት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላት በቅርቡ ወደሥራ የገቡ ሲሆን በሦስተኛ ዙርም 15 አዳዲስ ማዕከላት ለመገንባት መታቀዱ ተመላክቷል።


በክልሉ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሚዛን አማን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተገልጋዮች እንደገለጹት በማዕከሉ ቀልጣፋ፣ ከብልሹ አሰራር የጸዳና በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት እያገኙ ነው፡፡

ከተገልጋዮች መካከል አቶ ከረጋ ወልደማርያም በማዕከሉ የባንክ እና ዲጂታል መታወቂያን ጨምሮ የተለያዩ አገልግሎቶችን በተቀላጠፈ መስተንግዶ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።


የጤና ሙያ ፍቃድ ለማሳደስ ወደማዕከሉ እንደመጡ የገለጹት ወይዘሮ ቤዛዊት ጠና በበኩላቸው በማዕከሉ ባገኙት ቀልጣፋ መስተንግዶ በእጅጉ መደሰታቸውን ገልጸዋል።

ማዕከሉ ከመከፈቱ በፊት የጤና ሙያ ፍቃዳቸውን ለማደስ ረጅም ኪሎ ሜትር ይጓዙ እንደነበር አስታውሰው፣ በአሁኑ ወቅት አገልግሎቱን በአቅራቢያቸው ማግኘት መቻላቸው ትልቅ ለውጥ እንደሆነና ገንዘብና ወጪንም እንዳስቀረላቸው ተናግረዋል።

መንግስት ለሕዝብ የቀረበና ምቹ አገልግሎት ለመስጠት የጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰራርን ከማዘመን ባለፈ የጊዜና ጉልበት ብክነት ማስቀረቱን የገለጹት ደግሞ አቶ ስማቸው መኮንን እና ወጣት ሀፊዝ ሁሴን ናቸው።


ዲጂታል መታወቂያ ለማውጣት በማዕከሉ መገኘታቸውን ገልጸው፣ ከዚህ ቀደም ሲገጥማቸው የነበረ የቀጠሮ ምልልስና ሌሎች ችግሮች ተፈተው ፈጣንና ከሙስና የጸዳ አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ምክትል ሥራ አስፈጻሚ አቶ አህመዲን አወል በበኩላቸው መንግሥት የሕዝብ አገልግሎትን ከእንግልትና አድሏዊ አሠራር ነጻ ለማድረግ የዘረጋው ዘመናዊ አሠራር ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው።


በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከ35 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች አገልግሎት መስጠቱን ጠቅሰው የተገልጋይ ቁጥርና እርካታም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል ብለዋል።

በክልሉ የዲጂታል አሠራሩን በማስፋፋት ዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙና የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ በማለም በሁለተኛ ዙር 5 ተጨማሪ ማዕከላት ተገንብተው ሥራ መጀመራቸውን ገልጸዋል።

በማዕከላቱ እየተገኘ ያለውን ውጤት ለማስቀጠል የህዝብን ተጠቃሚነት ለማስቀጠል በሦስተኛ ዙር 15 አዳዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላት በተለያዩ የክልሉ ከተሞች በቅርቡ እንደሚገነቡም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስ...

Jul 7, 2026

የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ጥገናን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው

ኮምቦልቻ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፡- የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Jul 1, 2026

ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በረጅም ጊዜ የሚከፈል የብድር ስምምነ...

Jun 30, 2026

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በላቀ የአመራር ጥበብ ለመፈፀም በትኩረት እየተሰራ ነው- አቶ አረጋ ከበደ

ባሕር ዳር፤ ሰኔ 19/2018(ኢዜአ)፡- በተቋማት እየተካሄደ የሚገኘውን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በላቀ የአመራር ጥበብ በመፈፀም የመልካም አስ...

Jun 27, 2026