የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀልጣፋ አገልግሎት እያገኘን ነው

Jul 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሚዛን አማን፣ ሐምሌ 5/2018 (ኢዜአ)-:-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀልጣፋና ከሙስና የጸዳ አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን ተገልጋዮች ገለጹ፡፡

በክልሉ በሁለተኛ ዙር የተገነቡ አምስት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላት በቅርቡ ወደሥራ የገቡ ሲሆን በሦስተኛ ዙርም 15 አዳዲስ ማዕከላት ለመገንባት መታቀዱ ተመላክቷል።


በክልሉ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሚዛን አማን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተገልጋዮች እንደገለጹት በማዕከሉ ቀልጣፋ፣ ከብልሹ አሰራር የጸዳና በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት እያገኙ ነው፡፡

ከተገልጋዮች መካከል አቶ ከረጋ ወልደማርያም በማዕከሉ የባንክ እና ዲጂታል መታወቂያን ጨምሮ የተለያዩ አገልግሎቶችን በተቀላጠፈ መስተንግዶ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።


የጤና ሙያ ፍቃድ ለማሳደስ ወደማዕከሉ እንደመጡ የገለጹት ወይዘሮ ቤዛዊት ጠና በበኩላቸው በማዕከሉ ባገኙት ቀልጣፋ መስተንግዶ በእጅጉ መደሰታቸውን ገልጸዋል።

ማዕከሉ ከመከፈቱ በፊት የጤና ሙያ ፍቃዳቸውን ለማደስ ረጅም ኪሎ ሜትር ይጓዙ እንደነበር አስታውሰው፣ በአሁኑ ወቅት አገልግሎቱን በአቅራቢያቸው ማግኘት መቻላቸው ትልቅ ለውጥ እንደሆነና ገንዘብና ወጪንም እንዳስቀረላቸው ተናግረዋል።

መንግስት ለሕዝብ የቀረበና ምቹ አገልግሎት ለመስጠት የጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰራርን ከማዘመን ባለፈ የጊዜና ጉልበት ብክነት ማስቀረቱን የገለጹት ደግሞ አቶ ስማቸው መኮንን እና ወጣት ሀፊዝ ሁሴን ናቸው።


ዲጂታል መታወቂያ ለማውጣት በማዕከሉ መገኘታቸውን ገልጸው፣ ከዚህ ቀደም ሲገጥማቸው የነበረ የቀጠሮ ምልልስና ሌሎች ችግሮች ተፈተው ፈጣንና ከሙስና የጸዳ አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ምክትል ሥራ አስፈጻሚ አቶ አህመዲን አወል በበኩላቸው መንግሥት የሕዝብ አገልግሎትን ከእንግልትና አድሏዊ አሠራር ነጻ ለማድረግ የዘረጋው ዘመናዊ አሠራር ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው።


በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከ35 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች አገልግሎት መስጠቱን ጠቅሰው የተገልጋይ ቁጥርና እርካታም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል ብለዋል።

በክልሉ የዲጂታል አሠራሩን በማስፋፋት ዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙና የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ በማለም በሁለተኛ ዙር 5 ተጨማሪ ማዕከላት ተገንብተው ሥራ መጀመራቸውን ገልጸዋል።

በማዕከላቱ እየተገኘ ያለውን ውጤት ለማስቀጠል የህዝብን ተጠቃሚነት ለማስቀጠል በሦስተኛ ዙር 15 አዳዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላት በተለያዩ የክልሉ ከተሞች በቅርቡ እንደሚገነቡም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026