የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖርት ሉዊስ የጀመረው የቀጥታ በረራ በኢትዮጵያ እና በሞሪሸስ መካከል ያለውን ግንኙነት ያጠናክራል

Jul 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖርት ሉዊስ የጀመረው የቀጥታ በረራ በኢትዮጵያ እና በሞሪሸስ መካከል ያለውን ግንኙነት እንደሚያጠናክር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ገለጸ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ በመነሳት የመጀመሪያውን የቀጥታ በረራ ወደ ሞሪሽስ በሰር ሲውሳጉር ራምጉላም ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ደርሷል።

በሥነ ስርዓቱ ላይ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢቪዬሽን የሥራ አስፈፃሚዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የሕዝብ ተወካዮች በአውሮፕላን ማረፊያው ተገኝተዋል።

የበረራው መጀመርም በኢትዮጵያ እና በሞሪሸስ መካከል በቱሪዝም፣በንግድ፣ እና ኢንቨስትመንት እና በኢኮኖሚ መስኮች ያለውን ግንኙነት እንደሚያጠናክር ተገልጿል።

በዚህም አዳዲስ የትብብር ዕድሎች መፍጠር የሚያስችል መሆኑንም ተመላክቷል።

ይህ አዲሱ ቀጥታ በረራ በየሳምንቱ እሮብ፣ አርብ እና እሁድ በሳምንት ሦስት ቀናት የሚከናወን ሲሆን፤ የጉዞ ጊዜን በከፍተኛ ሁኔታ ከመቀነሱም በላይ መንገደኞች በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአዲስ አበባ ማዕከል በኩል ወደ ተለያዩ የአፍሪካ አገራትና የተቀረው የዓለም ክፍሎች ያለምንም እንግልት በቀላሉ እንዲገናኙ ያስችላል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የንግድ ዘርፍ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ለማ ያደቻ በዚሁ ወቅት፤ በኢትዮጵያና ሞሪሸስ መካከል አዲሱን ቀጥታ በረራ ለመጀመር በመቻሉ አየር መንገዱ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማው ተናግረዋል።

በረራው በሀገራቱ የንግድ ተቋማት መካከል ያለውን አጋርነት ከማጠናከር ባሻገር፣ በቱሪዝም፣ ኢንቨስትመንት እና የንግድ ልውውጥ ይበልጥ በማሳደግ ረገድ አዲስ ምዕራፍ ይከፍታል ብለዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን በውስጧ ካሉ ሀገራትና ከተቀረው ዓለም ጋር ለማገናኘት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ መሆኑንም ተናግረዋል።

የሞሪሸስ የቱሪዝም ሚኒስትር ክርስቲያን ሃሮልድ ሪቻርድ ዱቫል በበኩላቸው፤ የበረራው መጀመር በአፍሪካ የቱሪዝምና የትስስር ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ መክፈቻ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ይህ ቀጥታ በረራ ለቱሪዝም አዳዲስ ዕድሎችን እንደሚከፍት፣ የኢኮኖሚ ትብብርን እንደሚያጠናክር እና የአፍሪካ ሀገራትን ይበልጥ እንደሚያቀራርብም አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስ...

Jul 7, 2026

የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ጥገናን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው

ኮምቦልቻ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፡- የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Jul 1, 2026

ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በረጅም ጊዜ የሚከፈል የብድር ስምምነ...

Jun 30, 2026

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በላቀ የአመራር ጥበብ ለመፈፀም በትኩረት እየተሰራ ነው- አቶ አረጋ ከበደ

ባሕር ዳር፤ ሰኔ 19/2018(ኢዜአ)፡- በተቋማት እየተካሄደ የሚገኘውን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በላቀ የአመራር ጥበብ በመፈፀም የመልካም አስ...

Jun 27, 2026