የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ ለልማትና ለመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

Jul 18, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቡታጅራ፤ ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ ለህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት የገቢ ዕቅድ ተግባቦት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በቡታጅራ ከተማ እያካሄደ ነው።


በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል በዚህ ወቅት እንዳሉት፣ የክልሉን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ የህዝብን የልማትና የመልካም እስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ፡፡

በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የዘርፉ አመራር ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት ጠቅሰዋል፡፡

የገቢ አሰባሰብ ስራውን በልዩ ድጋፍና ክትትል በመምራት በዘርፉ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን በማረም በክልሉን ፈጣን እድገት ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡


የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ቀመሪያ ረሻድ በበኩላቸው ለክልሉ ህዝብ የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ገቢን በአግባቡ የመሰብሰብ ስራው በልዩ በትኩረት እየተመራ መሆኑን ተናግረዋል።

እንደ ኃላፊዋ ገለጻ በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት 27 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 26 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰብ ተችሏል።

ገቢው ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ9 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ጠቅሰው ለግብር ከፋዩ ማህበረሰብ የተፈጠረው ግንዛቤ፣ የገቢ አሰባሰቡ ወጥ በመደረጉ፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ መሰራቱ እና የድጋፍና ክትትል ስርዓት መጠናከሩ ለገቢው መጨመር አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

በተጀመረው የ2019 በጀት ዓመት 35 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማሰባሰብ መታቀዱንና ይህንንም ለማሳካት የግብር ህጉን የማስከበር እና በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

መንግሥት የሎጂስቲክስ ዘርፉን በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...

Jul 16, 2026

ሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስ...

Jul 7, 2026

የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ጥገናን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው

ኮምቦልቻ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፡- የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Jul 1, 2026

ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በረጅም ጊዜ የሚከፈል የብድር ስምምነ...

Jun 30, 2026