የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

አፍሪካ በተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት  አሜሪካ ዛሬ  ድጋፏን ታሳውቃለች

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2017 (ኢዜአ)፡- አፍሪካ በተባበሩት መንግስትት የጸጥታው ምክር ቤት ሁለት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት አሜሪካ ድጋፏን ኒውዮርክ በሚገኘው የድርጅቱ የውጭ ግንኙነት ምክር ቤት ዛሬ እንደምታሳውቅ በድርጅቱ የሜሪካ አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ-ግሪንፊልድ ገለጹ።

ከአፍሪካ በተጨማሪ አንድ ተዘዋዋሪ መቀመጫ ታዳጊ የደሴት (Highlands) ሀገራት እንዲኖራቸው አሜሪካ እንደምትደግፍ አምባሳደሯ መናገራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።

አገራቸው አፍሪካ በጸጥታ ምክር ቤቱ ቋሚ መቀመጫዎች እንዲኖራት ድጋፍ ማድረጓ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገውም አምባሳደሯ ጠቁመዋል።

የአፍሪካ ሕዝብ ከቢሊዮን በላይ ቢሆንም፣ እ.ኤ.አ. በ1946 የተቋቋመው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ለአኅጉሪቷ ቋሚ መቀመጫ ሳይሰጣት፣ ከ70 ዓመታት በላይ አስቆጥሯል፡፡

ምክር ቤቱ 15 አባላት ያሉት ሲሆን፤ ቋሚ መቀመጫ የሰጠው ግን ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት ያላቸው አምስቱ ሀገራት ለአሜሪካ፣ ለቻይና፣ ለፈረንሳይ፣ ለሩሲያና እንግሊዝ መሆኑን ጠቅሶ፣ድርድሮችን ለማበረታታት፣ ማዕቀብ ለመጣል፣ የሰላም አስከባሪ ማሰማራትን ጨምሮ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት ለማድረግ ውሳኔ የመስጠት ሥልጣን አለው።

በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅት ሁሉም የአፍሪካ አገሮች ከቅኝ ግዛት ነፃ ወጥተው በሂደት ተመድን ቢቀላቀሉም፣ ፀጥታው ምክር ቤት ካሉት አሥር ቋሚ ያልሆኑ መቀመጫዎች ለአፍሪካ የሰጠው ሦስት ተቀያያሪ መቀመጫዎችን እንደሆነም ዘገባው አመልክቷል፡፡

በግጭት የሚታመሱ አገሮች ያሉባት አፍሪካ፣ ድምጿ በቋሚነት እንዲሰማ፣ በሰላምና ፀጥታ ዘርፍ ጉልህ ሚና እንድትጫወት ዛሬ በምክር ቤቱ ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት፣ ለዚህም ተመድ የፀጥታውን ምክር ቤት መልሶ እንዲያዋቅር ስትወተውት ቆይታለች፡፡

እ.ኤ.አ. በ2010 አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት የአኅጉሪቱ መሪዎች ጥያቄ ቢያቀርቡም፣ ጥያቄያቸው እስካሁን መልስ አላገኘም፡፡

ሰኞ ነሐሴ 6 ቀን 2016 ዓ.ም የተመድ ከፍተኛ ባለሥልጣናት በነበራቸው ውይይትም፣ የድርጅቱ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬስ የፀጥታው ምክር ቤት ያረጀ አወቃቀሩን መልሶ እንዲያዋቅርና አፍሪካን በቋሚ አባልነት እንዲያካትት በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡

“ዓለም እየተለዋወጠች ባለችበት ወቅት አፍሪካ የምክር ቤት ቋሚ አባል መሆን አለባት፣ እስካሁን አለመወከሏም ትክክል አይደለም፤” ሲሉ የተናገሩት ጉተሬስ፣ በምክር ቤቱ ያለው ስብጥር አሁን እየተቀየረ ካለው ዓለም ጋር ተመጣጥኖ መሄድ አቅቶታል ብለዋል፡፡

“ከአንድ ቢሊዮን በላይ ሕዝብ የያዘን አኅጉር በቋሚነት ያላካተተ የሰላምና ፀጥታ አካል አንቀበልም፣ ሰላምና ደኅንነትን በተመለከተ የአፍሪካን አመለካከት ዋጋ የሚያሳጣ አንቀበልም” ሲሉም ለጉባዔው አሳስበዋል፡፡

አፍሪካ ዛሬ በምክር ቤቱ ሁለት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት ድጋፏን በአምባሳደሯ በኩል የምታሳውቀው አሜሪካ አፍሪካ በምክር ቤቱ ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት ብትደግፍም ድምጽን በድምጽ የመሻር መብት እንዲኖራት እንደማትፈቅድም ሊንዳ ቶማስ-ግሪንፊልድ መናገራቸውን ዘገባው አመላክቷል።

አፍሪካ በምክር ቤቱ ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት አሜሪካ መደገፏ አፍሪካ በምክር ቤቱ በቋሚነት ትወከል የሚለውን ዘመቻ እንደሚያግዘው አምባሰደሯ አስረድተዋል።

እንደ ሮይተርስ ዘገባ ምክር ቤቱ ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት ካላቸው ከአምስቱ ቋሚ አገሮች በተጨማሪ አሥር መቀመጫዎችን ለየቀጣናው ቢሰጥም፤ ሀገራቱ ቋሚ መቀመጫ የላቸውም፡፡

በምክር ቤቱ አፍሪካ ሦስት፣ እስያ ፖስፊክ ሁለት፣ ላቲን አሜሪካና ካሪቢያን ሁለት፣ ምዕራብ አውሮፓና ሌሎች ግዛቶች ሁለት እንዲሁም ምሥራቅ አውሮፓ አንድ መቀመጫ እንዳላቸው በመረጃው ተጠቅሷል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025