የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑ ተገለጸ።

በፕሮጀክቱ በመኩይ ወረዳ የተገነባው የወተት ማቀነባበሪያ ፋብሪካ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በዛሬው እለት ተመርቋል።


በቆላማ አካባቢ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የጋምቤላ ክልል አስተባበሪ ቤል ቢቾክ(ዶ/ር) በዘንድሮው በጀት ዓመት በፕሮጀክቱ በተለይም የትምህርትና የጤናን ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን አቅዶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም እስካሁን የሰባት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናቆ ለአገልገሎት እንዲበቁ መደረጉን ጠቅሰው በዛሬው እለት የተመረቀው የወተት ማቀነባበሪያ ፋብሪካም የዚሁ አካል መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይም ቀሪ ፕሮጀከቶችን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ጥረት የሚደረግ መሆኑን አረጋግጠዋል።


የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የመሰረተ ልማት አማካሪ ፒተር አማን፤ የቆላማ አካባቢ የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የክልሉን ልማትና የህዝቡን ተጠቀሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዛሬው እለት የተመረቀውን ጨምሮ ባለፉት ዓመታት በርካታ የማህበራዊና ኢኮኖያዊ ፋይዳ ያላቸውን ሰው ተኮር ፕሮጀከቶችን በማጠናነቅ አገልግሎት አንዲሰጡ ማድረጉንም አስታውሰዋል።


የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ብሩ በበኩላቸው የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክቱ የክልሉን የእንስሳት ሃብት የስጋና የወታት ተዋጽኦ ምርት ለማሳደግና የተሳለጠ የግብይት ስርዓት እንዲዘረጋ እያደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ ነው ብለዋል።

በፕሮጀክቱ ከአራት በላይ የእንስሳት 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ የግብይት ማዕከል፣ የወተትና የማር ማቀነባበሪያና ሌሎች ዘርፉን የሚያግዙ የመሰረተ ልማት አውታሮች መገንባቱን ጠቁመው ለበርካታ ወጣቶችም የስራ እድል መፍጠሩን ጠቅሰዋል።

በጋምቤላ ክልል የቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት በተመረጡ ዘጠኝ ወረዳዎች እየተተገበረ መሆኑ ታውቋል።

የቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት በቆላማ አካባቢዎች ያለውን ፀጋ በመጠቀም በተለይም የአርብቶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮችን የአኗኗር ዘይቤና የህይወት መንገድ የተቃና ለማድረግ የሚሰራ መሆኑ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025