የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑ ተገለጸ።

በፕሮጀክቱ በመኩይ ወረዳ የተገነባው የወተት ማቀነባበሪያ ፋብሪካ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በዛሬው እለት ተመርቋል።


በቆላማ አካባቢ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የጋምቤላ ክልል አስተባበሪ ቤል ቢቾክ(ዶ/ር) በዘንድሮው በጀት ዓመት በፕሮጀክቱ በተለይም የትምህርትና የጤናን ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን አቅዶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም እስካሁን የሰባት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናቆ ለአገልገሎት እንዲበቁ መደረጉን ጠቅሰው በዛሬው እለት የተመረቀው የወተት ማቀነባበሪያ ፋብሪካም የዚሁ አካል መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይም ቀሪ ፕሮጀከቶችን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ጥረት የሚደረግ መሆኑን አረጋግጠዋል።


የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የመሰረተ ልማት አማካሪ ፒተር አማን፤ የቆላማ አካባቢ የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የክልሉን ልማትና የህዝቡን ተጠቀሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዛሬው እለት የተመረቀውን ጨምሮ ባለፉት ዓመታት በርካታ የማህበራዊና ኢኮኖያዊ ፋይዳ ያላቸውን ሰው ተኮር ፕሮጀከቶችን በማጠናነቅ አገልግሎት አንዲሰጡ ማድረጉንም አስታውሰዋል።


የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ብሩ በበኩላቸው የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክቱ የክልሉን የእንስሳት ሃብት የስጋና የወታት ተዋጽኦ ምርት ለማሳደግና የተሳለጠ የግብይት ስርዓት እንዲዘረጋ እያደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ ነው ብለዋል።

በፕሮጀክቱ ከአራት በላይ የእንስሳት 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ የግብይት ማዕከል፣ የወተትና የማር ማቀነባበሪያና ሌሎች ዘርፉን የሚያግዙ የመሰረተ ልማት አውታሮች መገንባቱን ጠቁመው ለበርካታ ወጣቶችም የስራ እድል መፍጠሩን ጠቅሰዋል።

በጋምቤላ ክልል የቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት በተመረጡ ዘጠኝ ወረዳዎች እየተተገበረ መሆኑ ታውቋል።

የቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት በቆላማ አካባቢዎች ያለውን ፀጋ በመጠቀም በተለይም የአርብቶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮችን የአኗኗር ዘይቤና የህይወት መንገድ የተቃና ለማድረግ የሚሰራ መሆኑ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026