የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑ ተገለጸ።

በፕሮጀክቱ በመኩይ ወረዳ የተገነባው የወተት ማቀነባበሪያ ፋብሪካ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በዛሬው እለት ተመርቋል።


በቆላማ አካባቢ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የጋምቤላ ክልል አስተባበሪ ቤል ቢቾክ(ዶ/ር) በዘንድሮው በጀት ዓመት በፕሮጀክቱ በተለይም የትምህርትና የጤናን ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን አቅዶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም እስካሁን የሰባት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናቆ ለአገልገሎት እንዲበቁ መደረጉን ጠቅሰው በዛሬው እለት የተመረቀው የወተት ማቀነባበሪያ ፋብሪካም የዚሁ አካል መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይም ቀሪ ፕሮጀከቶችን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ጥረት የሚደረግ መሆኑን አረጋግጠዋል።


የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የመሰረተ ልማት አማካሪ ፒተር አማን፤ የቆላማ አካባቢ የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የክልሉን ልማትና የህዝቡን ተጠቀሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዛሬው እለት የተመረቀውን ጨምሮ ባለፉት ዓመታት በርካታ የማህበራዊና ኢኮኖያዊ ፋይዳ ያላቸውን ሰው ተኮር ፕሮጀከቶችን በማጠናነቅ አገልግሎት አንዲሰጡ ማድረጉንም አስታውሰዋል።


የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ብሩ በበኩላቸው የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክቱ የክልሉን የእንስሳት ሃብት የስጋና የወታት ተዋጽኦ ምርት ለማሳደግና የተሳለጠ የግብይት ስርዓት እንዲዘረጋ እያደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ ነው ብለዋል።

በፕሮጀክቱ ከአራት በላይ የእንስሳት 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ የግብይት ማዕከል፣ የወተትና የማር ማቀነባበሪያና ሌሎች ዘርፉን የሚያግዙ የመሰረተ ልማት አውታሮች መገንባቱን ጠቁመው ለበርካታ ወጣቶችም የስራ እድል መፍጠሩን ጠቅሰዋል።

በጋምቤላ ክልል የቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት በተመረጡ ዘጠኝ ወረዳዎች እየተተገበረ መሆኑ ታውቋል።

የቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት በቆላማ አካባቢዎች ያለውን ፀጋ በመጠቀም በተለይም የአርብቶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮችን የአኗኗር ዘይቤና የህይወት መንገድ የተቃና ለማድረግ የሚሰራ መሆኑ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026