የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ።

የዓባይ ተፋሰስ ሀገራት ትብብርን በሚያጠናክሩ ተግባራት ላይ አተኩረው እንዲሰሩም ፕሬዚዳንቱ አሳስበዋል።


19ኛው የናይል ቀን ''የናይል ትብብርን በማጎልበት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና ለጋራ ብልጽግና'' በሚል መሪ ሃሳብ በሳይንስ ሙዚየም ተከብሯል።

ፕሬዚዳንቱ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን የመልማት መብት የሚያረጋግጥና የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያሳድግ ነው።

ህዳሴ ግድብ ለተስተካከለ የውሃ አቅርቦት፣ የጎርፍ መጥለቅለቅንና ድርቅን ለመከላከል ትልቅ ዕድል መፍጠሩንም ተናግረዋል።


ከዚህም ባለፈ ግዙፍ የታዳሽ ኃይል ማመንጫ በመሆኑ የቀጣናው ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላል ነው ያሉት።

ዓባይ የእድገትና የተስፋ ምልክት ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ የዓባይ ተፋሰስ ሀገራት ድንበር ተሻጋሪ ውሃን ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ለመጠቀም በትብብር መስራት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል።


የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) በበኩላቸው የዓባይ ተፋሰስ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የጀመረቻቸው የአረንጓዴ አሻራና የተፋሰስ ልማት ሥራዎች ከራሷ አልፎ ለተፋሰሱ ሀገራት ጉልህ ጠቀሜታ እንዳላቸውም አንስተዋል።

የናይል ተፋሰስ ትብብርን ወደላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር የተፋሰሱ ሀገራት በኃላፊነት ስሜት እንዲሰሩም ጠይቀዋል።


የናይል ተፋሰስ ኢኒሼቲቭ ዋና ዳይሬክተር ፍሎሬንስ አዶንጎ(ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የናይል ቀን መከበሩ የተፋሰሱ ሀገራት ለጋራ ተጠቃሚነት ይበልጥ እንዲሰሩ የሚያደርግ ነው ብለዋል።

ድንበር ተሻጋሪ የውሃ ህብትን ቀጣይነት ባለው መልኩ ለማስተዳደርና ለማልማት ሀገራት ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩም ዋና ዳይሬክተሯ ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026