የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ።

የዓባይ ተፋሰስ ሀገራት ትብብርን በሚያጠናክሩ ተግባራት ላይ አተኩረው እንዲሰሩም ፕሬዚዳንቱ አሳስበዋል።


19ኛው የናይል ቀን ''የናይል ትብብርን በማጎልበት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና ለጋራ ብልጽግና'' በሚል መሪ ሃሳብ በሳይንስ ሙዚየም ተከብሯል።

ፕሬዚዳንቱ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን የመልማት መብት የሚያረጋግጥና የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያሳድግ ነው።

ህዳሴ ግድብ ለተስተካከለ የውሃ አቅርቦት፣ የጎርፍ መጥለቅለቅንና ድርቅን ለመከላከል ትልቅ ዕድል መፍጠሩንም ተናግረዋል።


ከዚህም ባለፈ ግዙፍ የታዳሽ ኃይል ማመንጫ በመሆኑ የቀጣናው ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላል ነው ያሉት።

ዓባይ የእድገትና የተስፋ ምልክት ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ የዓባይ ተፋሰስ ሀገራት ድንበር ተሻጋሪ ውሃን ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ለመጠቀም በትብብር መስራት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል።


የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) በበኩላቸው የዓባይ ተፋሰስ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የጀመረቻቸው የአረንጓዴ አሻራና የተፋሰስ ልማት ሥራዎች ከራሷ አልፎ ለተፋሰሱ ሀገራት ጉልህ ጠቀሜታ እንዳላቸውም አንስተዋል።

የናይል ተፋሰስ ትብብርን ወደላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር የተፋሰሱ ሀገራት በኃላፊነት ስሜት እንዲሰሩም ጠይቀዋል።


የናይል ተፋሰስ ኢኒሼቲቭ ዋና ዳይሬክተር ፍሎሬንስ አዶንጎ(ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የናይል ቀን መከበሩ የተፋሰሱ ሀገራት ለጋራ ተጠቃሚነት ይበልጥ እንዲሰሩ የሚያደርግ ነው ብለዋል።

ድንበር ተሻጋሪ የውሃ ህብትን ቀጣይነት ባለው መልኩ ለማስተዳደርና ለማልማት ሀገራት ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩም ዋና ዳይሬክተሯ ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026