አዲስ አበባ፤ ህዳር 18/2017(ኢዜአ)፦ በሶማሊያ ፓርላማ ዛሬ ከፍተኛ ብጥብጥ ተከስቷል።
የሶማሊያ መንግስት አካሄድን የተቃወሙ የሀገሪቱ የፓርላማ አባላት ቁጣቸውን በፓርላማ ውስጥ ሲገልጹ ታይተዋል።
የሶማሊያ ፓርላማ ባወጣው መግለጫ የሀገሪቱ መንግሥት የሶማሊያ ጦር አልሸባብን ከመዋጋት ይልቅ በጎሳ ክፍፍል እንዲወጠር በማድረግ የያዛቸውን ቦታዎች እንኳ እንዳያስተዳድር አድርጓል ብሏል።
በሀገሪቱ ሙስና ስር እየሰደደ ከመምጣቱም ባሻገር መንግስት ጦሩን ለፖለቲካ ፍጆታ እየተጠቀመ መሆኑንም ነው ፓርላማው በመግለጫው ያስታወቀው።
ይህም በሀገሪቱ የጎሳ ክፍፍል እንዲፈጠር እያደረገ መሆኑንም አስታውቋል።
ከሶማሊያ ህገ መንግስት ባፈነገጠ መልኩ የሀገሪቱ መንግስት የክልላዊ አስተዳደሮችን መብቶች እየተጋፋ መሆኑንም እንዲሁ።
የሶማሊያ መንግስት ሶማሊያውያንን በጎሳ ለመከፋፈል የሚያደርገው ሙከራ በአስቸኳይ እንዲቆምም ጠይቀዋል።
የሀገሪቱ መንግስት ከመሰል አደገኛ አካሄዱ ካላቆመም ሶማሊያ የመፍረስ አደጋ እንደሚገጥማት የፓርላማ አባላቱ ባወጡት መግለጫ አስጠንቅቀዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025