
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 27/2017(ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ሰሞኑን እየተከሰተ ባለው የመሬት መንቀጥቀጥና ንዝረት በተመለከተ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉ ምሁራን ጋር ተወያዩ፡፡
ከንቲባዋ ሰሞኑን በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ስለተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ እና ንዝረት እንዲሁም አጠቃላይ ስርጭቱን በተመለከተ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስ፣ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም እንዲሁም ከጂኦሎጂካል ሰርቬይ ከመጡ ምሁራን ጋር ተወያይተናል ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡

በውይይታችንም ምሁራኑ ጥናቶችን ያቀረቡልን ሲሆን ጥናቶቹ እንደሚያሳዩት በአዲስ አበባ በአሁኑ ሰዓት በአፋር እና አካባቢው እያጋጠመን ካለው የመሬት መንቀጥቀጥ የተነሳ የመሬት ንዝረት እያጋጠመ መሆኑን ገልፀው ንዝረቱ ሲያጋጥም መደናገጥ እና መረበሽ ሳያስፈልግ በባለሙያዎች የሚሰጡ ምክሮችን በመከታተል መረጋጋት እንደሚገባ አስረድተውናል ብለዋል።
ቢሆንም ከተማችን አዲስ አበባ ወደፊት ተጋላጭነት ያላት በመሆኑ የምንችለውን ተገቢውን ጥንቃቄ ከወዲሁ ማድረግ እንዲያስችል ለአንዳንድ ቅድመ ጥንቃቄ የሚረዱ ጥናቶችን ለማድረግ የባለሙያዎች ግብረ ሀይል በማደራጀት በጋራ ለመስራት ተስማምተናል ነው ያሉት በመልዕክታቸው።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025