
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 27/2017(ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ሰሞኑን እየተከሰተ ባለው የመሬት መንቀጥቀጥና ንዝረት በተመለከተ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉ ምሁራን ጋር ተወያዩ፡፡
ከንቲባዋ ሰሞኑን በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ስለተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ እና ንዝረት እንዲሁም አጠቃላይ ስርጭቱን በተመለከተ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስ፣ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም እንዲሁም ከጂኦሎጂካል ሰርቬይ ከመጡ ምሁራን ጋር ተወያይተናል ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡

በውይይታችንም ምሁራኑ ጥናቶችን ያቀረቡልን ሲሆን ጥናቶቹ እንደሚያሳዩት በአዲስ አበባ በአሁኑ ሰዓት በአፋር እና አካባቢው እያጋጠመን ካለው የመሬት መንቀጥቀጥ የተነሳ የመሬት ንዝረት እያጋጠመ መሆኑን ገልፀው ንዝረቱ ሲያጋጥም መደናገጥ እና መረበሽ ሳያስፈልግ በባለሙያዎች የሚሰጡ ምክሮችን በመከታተል መረጋጋት እንደሚገባ አስረድተውናል ብለዋል።
ቢሆንም ከተማችን አዲስ አበባ ወደፊት ተጋላጭነት ያላት በመሆኑ የምንችለውን ተገቢውን ጥንቃቄ ከወዲሁ ማድረግ እንዲያስችል ለአንዳንድ ቅድመ ጥንቃቄ የሚረዱ ጥናቶችን ለማድረግ የባለሙያዎች ግብረ ሀይል በማደራጀት በጋራ ለመስራት ተስማምተናል ነው ያሉት በመልዕክታቸው።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026