መቱ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- በኢሉአባቦር ዞን በአርሶ አደሮች ተሳትፎ ከ11 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።
የጽሕፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ መልካሙ ጫሊ ለኢዜአ እንደገለጹት የተፈጥሮ ማዳበሪያው እየተዘጋጀ ያለው በዞኑ ዘጠኝ ወረዳዎች ነው።
የተፈጥሮ ማዳበሪያው በአካባቢ ከሚገኙ ግብአቶች እንደሚዘጋጅ ጠቅሰው ይህም የአፈር ለምነትና እርጥበት በመጨመር ምርታማነትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል አስረድተዋል።
ለስራው ስኬታማነት በወረዳዎቹ የ'ቨርም ኮምፖስት' ማዘጋጃ ማዕከላት ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ሲሆን ስራውም በግብርና ልማት ጣቢያ ባለሙያዎች ምክረ ሃሳብ ተደግፎ እየተከናወነ ነው ብለዋል።
የተፈጥሮ ማዳበሪያ የመሬት ለምነትንና አርጥበትን ለረዥም ጊዜ ጠብቆ በማቆየት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ የተሳታፊ አርሶ አደሮች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱንም አብራርተዋል።
ከዞኑ አርሶ አደሮች መካከል አቶ ታደሰ አምቢሳ እንደሚሉት የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት ለመኽር እርሻ ልማት በማዋል ምርታቸውን በማሳደግ ላይ ናቸው።
ሌላኛው አርሶ አደር አዲሱ ተፈሪ በበኩላቸው ከፍግና ከዕፅዋት ብስባሽ የሚያዘጋጁት የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለአፈር ለምነት ከፍተኛ ጠቀሜታ ስላለው በስፋት እያዘጋጁ መሆኑን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅትም በቀያቸው ለመጪው መኸር እርሻ የሚያስፈልጋቸውን የተፈጥሮ ማዳበሪያ የማዘጋጀት ስራ መጀመራቸውን አስታውቀዋል።
አርሶ አደር ጌታቸው ጊጆ በበኩቸው፣ የማሳቸውን ለምነት በመጠበቅ ምርትና ምርታማነታቸውን ለመጨመር የተፈጥሮ ማዳበሪያ የማዘጋጀት ልምድ ማዳበራቸውን ይገልጻሉ።
በተለይ በወረዳው ከተሰራው የቨርም ኮምፖስት ማምረቻ ማዕከል የተሻለ ልምድና ተሞክሮ እየቀሰሙ መሆናቸውን ገልጸው ይህም ይበልጥ በዝግጅቱ እንዲቀጥሉበት አቅም እንደፈጠረላቸው አስረድተዋል።
የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት ምርታማነትን ከማሳደግ ባሻገር ቀደም ሲል ለሰው ሰራሽ ማዳበሪያ መግዣ ሲያወጡ የነበረውን ወጪ በግማሽ ለመቀነስ እንዳስቻላቸው ነው አርሶ አደሮቹ የተናገሩት።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025