
መቱ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- በኢሉአባቦር ዞን በአርሶ አደሮች ተሳትፎ ከ11 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

የጽሕፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ መልካሙ ጫሊ ለኢዜአ እንደገለጹት የተፈጥሮ ማዳበሪያው እየተዘጋጀ ያለው በዞኑ ዘጠኝ ወረዳዎች ነው።
የተፈጥሮ ማዳበሪያው በአካባቢ ከሚገኙ ግብአቶች እንደሚዘጋጅ ጠቅሰው ይህም የአፈር ለምነትና እርጥበት በመጨመር ምርታማነትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል አስረድተዋል።
ለስራው ስኬታማነት በወረዳዎቹ የ'ቨርም ኮምፖስት' ማዘጋጃ ማዕከላት ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ሲሆን ስራውም በግብርና ልማት ጣቢያ ባለሙያዎች ምክረ ሃሳብ ተደግፎ እየተከናወነ ነው ብለዋል።
የተፈጥሮ ማዳበሪያ የመሬት ለምነትንና አርጥበትን ለረዥም ጊዜ ጠብቆ በማቆየት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ የተሳታፊ አርሶ አደሮች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱንም አብራርተዋል።

ከዞኑ አርሶ አደሮች መካከል አቶ ታደሰ አምቢሳ እንደሚሉት የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት ለመኽር እርሻ ልማት በማዋል ምርታቸውን በማሳደግ ላይ ናቸው።
ሌላኛው አርሶ አደር አዲሱ ተፈሪ በበኩላቸው ከፍግና ከዕፅዋት ብስባሽ የሚያዘጋጁት የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለአፈር ለምነት ከፍተኛ ጠቀሜታ ስላለው በስፋት እያዘጋጁ መሆኑን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅትም በቀያቸው ለመጪው መኸር እርሻ የሚያስፈልጋቸውን የተፈጥሮ ማዳበሪያ የማዘጋጀት ስራ መጀመራቸውን አስታውቀዋል።
አርሶ አደር ጌታቸው ጊጆ በበኩቸው፣ የማሳቸውን ለምነት በመጠበቅ ምርትና ምርታማነታቸውን ለመጨመር የተፈጥሮ ማዳበሪያ የማዘጋጀት ልምድ ማዳበራቸውን ይገልጻሉ።
በተለይ በወረዳው ከተሰራው የቨርም ኮምፖስት ማምረቻ ማዕከል የተሻለ ልምድና ተሞክሮ እየቀሰሙ መሆናቸውን ገልጸው ይህም ይበልጥ በዝግጅቱ እንዲቀጥሉበት አቅም እንደፈጠረላቸው አስረድተዋል።
የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት ምርታማነትን ከማሳደግ ባሻገር ቀደም ሲል ለሰው ሰራሽ ማዳበሪያ መግዣ ሲያወጡ የነበረውን ወጪ በግማሽ ለመቀነስ እንዳስቻላቸው ነው አርሶ አደሮቹ የተናገሩት።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026