የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በኢሉአባቦር ዞን በአርሶ አደሮች ተሳትፎ ከ11 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ እየተዘጋጀ ነው

Jan 13, 2025

IDOPRESS

መቱ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- በኢሉአባቦር ዞን በአርሶ አደሮች ተሳትፎ ከ11 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።


የጽሕፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ መልካሙ ጫሊ ለኢዜአ እንደገለጹት የተፈጥሮ ማዳበሪያው እየተዘጋጀ ያለው በዞኑ ዘጠኝ ወረዳዎች ነው።

የተፈጥሮ ማዳበሪያው በአካባቢ ከሚገኙ ግብአቶች እንደሚዘጋጅ ጠቅሰው ይህም የአፈር ለምነትና እርጥበት በመጨመር ምርታማነትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል አስረድተዋል።

ለስራው ስኬታማነት በወረዳዎቹ የ'ቨርም ኮምፖስት' ማዘጋጃ ማዕከላት ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ሲሆን ስራውም በግብርና ልማት ጣቢያ ባለሙያዎች ምክረ ሃሳብ ተደግፎ እየተከናወነ ነው ብለዋል።

የተፈጥሮ ማዳበሪያ የመሬት ለምነትንና አርጥበትን ለረዥም ጊዜ ጠብቆ በማቆየት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ የተሳታፊ አርሶ አደሮች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱንም አብራርተዋል።


ከዞኑ አርሶ አደሮች መካከል አቶ ታደሰ አምቢሳ እንደሚሉት የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት ለመኽር እርሻ ልማት በማዋል ምርታቸውን በማሳደግ ላይ ናቸው።

ሌላኛው አርሶ አደር አዲሱ ተፈሪ በበኩላቸው ከፍግና ከዕፅዋት ብስባሽ የሚያዘጋጁት የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለአፈር ለምነት ከፍተኛ ጠቀሜታ ስላለው በስፋት እያዘጋጁ መሆኑን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅትም በቀያቸው ለመጪው መኸር እርሻ የሚያስፈልጋቸውን የተፈጥሮ ማዳበሪያ የማዘጋጀት ስራ መጀመራቸውን አስታውቀዋል።

አርሶ አደር ጌታቸው ጊጆ በበኩቸው፣ የማሳቸውን ለምነት በመጠበቅ ምርትና ምርታማነታቸውን ለመጨመር የተፈጥሮ ማዳበሪያ የማዘጋጀት ልምድ ማዳበራቸውን ይገልጻሉ።

በተለይ በወረዳው ከተሰራው የቨርም ኮምፖስት ማምረቻ ማዕከል የተሻለ ልምድና ተሞክሮ እየቀሰሙ መሆናቸውን ገልጸው ይህም ይበልጥ በዝግጅቱ እንዲቀጥሉበት አቅም እንደፈጠረላቸው አስረድተዋል።

የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት ምርታማነትን ከማሳደግ ባሻገር ቀደም ሲል ለሰው ሰራሽ ማዳበሪያ መግዣ ሲያወጡ የነበረውን ወጪ በግማሽ ለመቀነስ እንዳስቻላቸው ነው አርሶ አደሮቹ የተናገሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026