
አዲስ አበባ፤ጥር 3/2017(ኢዜአ)፦ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ብቁና ተወዳዳሪ የሳይበር ባለሙያ ማፍራት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ገለጸ።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በሰመር ካምፕ መርሃ-ግብር ያሰለጠናቸውን 337 ባለተሰጥኦ ታዳጊዎች አስመርቋል።
የአስተዳደሩ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዳንኤል ጉታ በዚሁ ጊዜ፥ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ብቃት ያለው የሳይበር ባለሙያ በብዛትና በጥራት ማፍራት ያስፈልጋል ብለዋል።
አስተዳደሩ ከመላ ኢትዮጵያ የተወጣጡ ባለልዩ ተሰጥኦ ታዳጊዎችን በሳይበርና ተያያዥ ዘርፎች እያበቃ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
ተለዋዋጭ የቴክኖሎጂ ዕድገትን የሚመጥንና የሳይበር ጥቃት ለመከላከል ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያ የማፍራት ጥረቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም ነው ያነሱት።
በአስተዳደሩ የሳይበር ማዕከል ዳይሬክተር ቢሻው በየነ በበኩላቸው፥ ከአገራዊ ለውጡ በኃላ ለባለተሰጥኦ ወጣቶች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በዚህም ማዕከሉ ከሳይበር ደህንነት ጋር በተያያዘ የሚሰጠው ስልጠና ተደራሽነት ለማስፋት ጥረት እያደረገ መሆኑን አንስተዋል።
የመከላከያ ሳይበር ዳይሬክተር ብርጋዴር ጄኔራል ደረጀ ደመቀ እንዲሁም የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ደረጀ እንግዳ(ዶ/ር) በበኩላቸው ኢትዮጵያን የሚመጥን ጠንካራ የሳይበር ባለሙያ ግንባታ በሁሉም ዘርፎች ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
የትምህርትና ሌሎች ተቋማትም የባለተሰጥኦ ወጣቶችን አቅም መጠቀም ላይ በትኩረት መስራት እንዳለባቸው ነው ያነሱት።
ከሰልጣኞቹ መካከል ዳዊት ከተማና ዳንኤል ቢፍቱ በበኩላቸው በስልጠናው መሰረታዊ የዲጅታል ዕውቀት ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል።

ችግር ፈቺ የፈጠራ ውጤቶችን በማፍለቅ አገርና ህዝባቸውን ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውንም አመልክተዋል።
በተመሳሳይ አስተዳደሩ የአምስት ሚሊየን ኮደርስ ኢኒሼቲቭን በቅዳሜና እሁድ የስልጠና ፕሮግራም ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች ለተወጣጡ 40 ተማሪዎች መስጠት ጀምሯል።
ስልጠናውን ለመውሰድ ያለው ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱም ነው የተገለጸው።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026