
አዲስ አበባ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- በመጪው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ ለሚሳተፉ እንግዶች የኢትዮጵያን የቱሪዝም ሀብቶች ማስተዋወቅና ማስጎብኘት የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል።
38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ የካቲት 8 እና 9 ቀን 2017 ዓ.ም፣ 46ኛው የሕብረቱ የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ደግሞ የካቲት 5 እና 6 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ይታወቃል።
በህብረቱ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ የሀገራት መሪዎች፣ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ የአለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎችን ጨምሮ ሌሎች በርካታ እንግዶች ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ።

ይህን መነሻ በማድረግ የቱሪዝም ሚኒስቴር ለጉባኤው ታዳሚዎች የቱሪዝም ሀብቶችን ለማስተዋወቅና ለማስጎብኘት እየተደረጉ ያሉ ቅድመ ዝግጅቶችን ለኢዜአ ገልጿል።
የቱሪዝም ሚኒስቴር የኮሙኒኬሽን እና የህዝብ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ አለማየሁ ጌታቸው ኢትዮጵያ የሚዳሰሱ እና የማይዳሰሱ እምቅ የቱሪዝም መዳረሻ ቦታዎች ያሏት እና በልዩ ልዩ ባህሎች የታደለች ሀገር መሆኗን ጠቅሰዋል።
እነዚህን እምቅ የቱሪዝም ሀብቶች በጉባኤው ላይ ለሚሳተፉ እንግዶች ማስተዋወቅና ማስጎብኘት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
እየተከናወኑ ካሉ ዝግጅቶች መካከል አስጎብኚ ድርጅቶች የጉብኝት ፓኬጆችን ቀድመው እንዲያዘጋጁ ማድረግ አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል።

አዳዲስ የተገነቡ እና ነባር የቱሪዝም መዳረሻዎችን በቴክኖሎጂ በተደገፈ መልኩ ለተሳታፊዎች እንዲቀርቡ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
የጉባኤውን ምቹ አጋጣሚ በአግባቡ ለመጠቀም ሚኒስቴሩ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት እየሰራ እንገደሚገኝ ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ በርካታ አለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ስብሰባዎች እየተስተናገዱ መምጣቱ የሀገሪቱን የቱሪዝም ሀብቶች እንዲጎበኙ መልካም እድል መፍጠሩንም ጠቁመዋል።
ለአፍሪካ ህብረት ጉባኤ የሚመጡ እንግዶችንም በአግባቡ በለማስተናገድ የዘርፉ ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ አስገንዝበዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025