

የካፒታል ገበያ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ገበያ መሪ ተዋናይ እንድትሆን ያስችላታል፤

ዘርፉ ሁሉንም በንቃት በማሳተፍ ምርትና አገልግሎቶችን በስፋት ማቅረብ ያስችላል፤

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በቴክኖሎጂ የሚታገዝ በመሆኑ ለሥራ እድል ፈጠራ እና ለኢኮኖሚ እድገት ገንቢ ሚና ይጫወታል፤

የባንኮችን ተቀማጭ ገንዘብ ለማሳደግ ወሳኝ ነው፤

የቁጠባ መጠንን ማሳደግና ፕራይቬታይዜሽንን ማጠናከር ለካፒታል ገበያ አስፈላጊ ናቸው፤

የሀገር ውስጥ ኢንቨስተሮች ገበያውን ከደገፉት በሀገር ውስጥ አቅም ኢኮኖሚውን ማጠናከር ያስችላል፤

ጠንካራ የካፒታል ገበያ መኖር በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ ኢኮኖሚ ለመገንባት ይረዳል፤

ትልቅ ትኩረት፤ ገበያውን የሚመራና የሚቆጣጣር ግልጽ የካፒታል ገበያ የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት ለካፒታል ገበያ ዕድገት ወሳኝ ነው፤

የካፒታል ገበያ ጥቅል የሀገርን ኢኮኖሚ የሚደግፍ እና የዜጎችን ህይወት የሚቀይር ዘርፍ ነው፤

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ የተለያዩ የንግድ አይነቶችን ታሳቢ በማድረግ ሶስት የተለያዩ የገበያ አይነቶችን ማለትም የአክሲዮን ገበያ፣ የዕዳ ሰነድ ገበያ እና የአማራጭ ገበያን የሚያቀርብ ነው።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026