አዲስ አበባ፤ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡-ባለፉት ስድስት ወራት በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የተቀዱ 77 ቴክኖሎጂዎችን ወደ ኢንተርፕራይዞች ማሸጋገር መቻሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ።
ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራ ለማህበረሰቡ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው ሲሆን የሚፈጠሩ ቴክኖሎጂዎች ደግሞ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በማኑፋክቸሪንግና ዘርፎች የሚስተዋሉ ችግሮችን ሊፈቱ ይገባል።
በዚህ ረገድ ቢሮው ከተሰጠው ተልዕኮ አኳያ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን በመቅዳት የማሸጋገር ስራዎች ላይ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
በቢሮው የቴክኖሎጂና የኢንተርፕራይዝ ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ መሃመድ ልጋኔ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት 77 ቴክኖሎጂዎችን በመቅዳት ወደ ኢንተርፕራይዞች ማሸጋገር መቻሉን ጠቅሰዋል።
ቴክኖሎጂን ከመቅዳት ባለፈ ለኢንተርፕራይዞች በማሸጋገር ውጤት እንዲመዘገብ የተሻለ ስራ መሰራቱን አስታውቀዋል።
በዚህም በማምረቻ 26 ፣ በምርት ቴክኖሎጂ 40 ፣ በሀገር በቀል ቴክኖሎጂ 6፣ በአይሲቲ 13 በድምሩ 85 ቴክኖሎጂዎችን የመቅዳት ስራ ተሰርቷል ነው ያሉት።
ኢንተርፕራይዞቹ በተደረገላቸው ድጋፍና ክትትል በአዲስ መንገድ ማምረት በመቻላቸው የተሻለ ውጤት ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል።
በቀጣይ ስድስት ወራት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ነው ምክትል ቢሮ ሃላፊው የተናገሩት።
የተቀዱ ቴክኖሎጂዎችን በአውደ ርዕዮች ላይ በማቅረብ ኢንተርፕራይዞቹ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025