
አዲስ አበባ፤ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡-ባለፉት ስድስት ወራት በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የተቀዱ 77 ቴክኖሎጂዎችን ወደ ኢንተርፕራይዞች ማሸጋገር መቻሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ።
ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራ ለማህበረሰቡ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው ሲሆን የሚፈጠሩ ቴክኖሎጂዎች ደግሞ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በማኑፋክቸሪንግና ዘርፎች የሚስተዋሉ ችግሮችን ሊፈቱ ይገባል።

በዚህ ረገድ ቢሮው ከተሰጠው ተልዕኮ አኳያ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን በመቅዳት የማሸጋገር ስራዎች ላይ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
በቢሮው የቴክኖሎጂና የኢንተርፕራይዝ ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ መሃመድ ልጋኔ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት 77 ቴክኖሎጂዎችን በመቅዳት ወደ ኢንተርፕራይዞች ማሸጋገር መቻሉን ጠቅሰዋል።

ቴክኖሎጂን ከመቅዳት ባለፈ ለኢንተርፕራይዞች በማሸጋገር ውጤት እንዲመዘገብ የተሻለ ስራ መሰራቱን አስታውቀዋል።
በዚህም በማምረቻ 26 ፣ በምርት ቴክኖሎጂ 40 ፣ በሀገር በቀል ቴክኖሎጂ 6፣ በአይሲቲ 13 በድምሩ 85 ቴክኖሎጂዎችን የመቅዳት ስራ ተሰርቷል ነው ያሉት።
ኢንተርፕራይዞቹ በተደረገላቸው ድጋፍና ክትትል በአዲስ መንገድ ማምረት በመቻላቸው የተሻለ ውጤት ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል።
በቀጣይ ስድስት ወራት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ነው ምክትል ቢሮ ሃላፊው የተናገሩት።
የተቀዱ ቴክኖሎጂዎችን በአውደ ርዕዮች ላይ በማቅረብ ኢንተርፕራይዞቹ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025