
አዲስ አበባ፤ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡-ባለፉት ስድስት ወራት በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የተቀዱ 77 ቴክኖሎጂዎችን ወደ ኢንተርፕራይዞች ማሸጋገር መቻሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ።
ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራ ለማህበረሰቡ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው ሲሆን የሚፈጠሩ ቴክኖሎጂዎች ደግሞ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በማኑፋክቸሪንግና ዘርፎች የሚስተዋሉ ችግሮችን ሊፈቱ ይገባል።

በዚህ ረገድ ቢሮው ከተሰጠው ተልዕኮ አኳያ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን በመቅዳት የማሸጋገር ስራዎች ላይ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
በቢሮው የቴክኖሎጂና የኢንተርፕራይዝ ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ መሃመድ ልጋኔ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት 77 ቴክኖሎጂዎችን በመቅዳት ወደ ኢንተርፕራይዞች ማሸጋገር መቻሉን ጠቅሰዋል።

ቴክኖሎጂን ከመቅዳት ባለፈ ለኢንተርፕራይዞች በማሸጋገር ውጤት እንዲመዘገብ የተሻለ ስራ መሰራቱን አስታውቀዋል።
በዚህም በማምረቻ 26 ፣ በምርት ቴክኖሎጂ 40 ፣ በሀገር በቀል ቴክኖሎጂ 6፣ በአይሲቲ 13 በድምሩ 85 ቴክኖሎጂዎችን የመቅዳት ስራ ተሰርቷል ነው ያሉት።
ኢንተርፕራይዞቹ በተደረገላቸው ድጋፍና ክትትል በአዲስ መንገድ ማምረት በመቻላቸው የተሻለ ውጤት ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል።
በቀጣይ ስድስት ወራት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ነው ምክትል ቢሮ ሃላፊው የተናገሩት።
የተቀዱ ቴክኖሎጂዎችን በአውደ ርዕዮች ላይ በማቅረብ ኢንተርፕራይዞቹ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026