
አዲስ አበባ፤ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡-ባለፉት ስድስት ወራት በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የተቀዱ 77 ቴክኖሎጂዎችን ወደ ኢንተርፕራይዞች ማሸጋገር መቻሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ።
ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራ ለማህበረሰቡ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው ሲሆን የሚፈጠሩ ቴክኖሎጂዎች ደግሞ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በማኑፋክቸሪንግና ዘርፎች የሚስተዋሉ ችግሮችን ሊፈቱ ይገባል።

በዚህ ረገድ ቢሮው ከተሰጠው ተልዕኮ አኳያ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን በመቅዳት የማሸጋገር ስራዎች ላይ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
በቢሮው የቴክኖሎጂና የኢንተርፕራይዝ ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ መሃመድ ልጋኔ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት 77 ቴክኖሎጂዎችን በመቅዳት ወደ ኢንተርፕራይዞች ማሸጋገር መቻሉን ጠቅሰዋል።

ቴክኖሎጂን ከመቅዳት ባለፈ ለኢንተርፕራይዞች በማሸጋገር ውጤት እንዲመዘገብ የተሻለ ስራ መሰራቱን አስታውቀዋል።
በዚህም በማምረቻ 26 ፣ በምርት ቴክኖሎጂ 40 ፣ በሀገር በቀል ቴክኖሎጂ 6፣ በአይሲቲ 13 በድምሩ 85 ቴክኖሎጂዎችን የመቅዳት ስራ ተሰርቷል ነው ያሉት።
ኢንተርፕራይዞቹ በተደረገላቸው ድጋፍና ክትትል በአዲስ መንገድ ማምረት በመቻላቸው የተሻለ ውጤት ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል።
በቀጣይ ስድስት ወራት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ነው ምክትል ቢሮ ሃላፊው የተናገሩት።
የተቀዱ ቴክኖሎጂዎችን በአውደ ርዕዮች ላይ በማቅረብ ኢንተርፕራይዞቹ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026