የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>የተባበሩት አረብ ኤምሬቶቹ ሪች ዲጂታል በኢትዮጵያ የአይሲቲ ዘርፍ መዋዕለ ንዋዩን የማፍሰስ ፍላጎት እንዳለው ገለጸ</p>

Jan 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡-የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽንና ቴክኖሎጂ ተቋም ሪች ዲጂታል (REACH Digital) በኢትዮጵያ በዘርፉ መዋዕለ ንዋዩን የማፍሰስ ጠንካራ ፍላጎት እንዳለው አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ገሰሰ (ዶ/ር) ከሪች ዲጂታል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል።

በውይይቱ ወቅት ኮሚሽነሩ ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽንና ቴክኖሎጂ ጨምሮ ኢትዮጵያ በተለያዩ ቁልፍ ዘርፎች ያላትን ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጭ አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት የግሉ ዘርፍ በሀገሪቷ ኢኮኖሚ ያለውን ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያስችሉ የተለያዩ ሪፎርሞችን እያደረገ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

የአይሲቲውን ዘርፍ የሚያሳድጉ ጠንካራ የፖሊሲ ማዕቀፎች መኖራቸውን የገለጹት ኮሚሽነሩ፥ፖሊሲው መንግስት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትምንት ለመሳብ እየተገበራቸው ከሚገኙ ኢኒሼቲቮች ጋር የተቆራኘ መሆኑን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ክህሎት ያለው የሰው ኃይል፣ ኢነርጂ፣ ኢንተርኔት እና የአይሲቲ ፓርኮችን ጨምሮ የመሰረተ ልማቶች አቅርቦት እንዲሁ የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ የገበያ አቅም እንዳላት አስረድተዋል።

ሪች ዲጂታል ምቹ እድሎቹን በመጠቀም በዘርፉ እንዲሰማራ ኮሚሽነሩ ጥሪ አቅርበዋል።

የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽንና ቴክኖሎጂ ተቋም ሪች ዲጂታል (REACH Digital) ተወካዮች በበኩላቸው ተቋሙ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋዩን የማፍሰስ ጠንካራ ፍላጎት እንዳለው ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ለአይሲቲ ልማት አመቺ ምህዳር እንዳለ መናገራቸውን ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025