
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡-የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽንና ቴክኖሎጂ ተቋም ሪች ዲጂታል (REACH Digital) በኢትዮጵያ በዘርፉ መዋዕለ ንዋዩን የማፍሰስ ጠንካራ ፍላጎት እንዳለው አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ገሰሰ (ዶ/ር) ከሪች ዲጂታል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል።
በውይይቱ ወቅት ኮሚሽነሩ ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽንና ቴክኖሎጂ ጨምሮ ኢትዮጵያ በተለያዩ ቁልፍ ዘርፎች ያላትን ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጭ አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት የግሉ ዘርፍ በሀገሪቷ ኢኮኖሚ ያለውን ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያስችሉ የተለያዩ ሪፎርሞችን እያደረገ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
የአይሲቲውን ዘርፍ የሚያሳድጉ ጠንካራ የፖሊሲ ማዕቀፎች መኖራቸውን የገለጹት ኮሚሽነሩ፥ፖሊሲው መንግስት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትምንት ለመሳብ እየተገበራቸው ከሚገኙ ኢኒሼቲቮች ጋር የተቆራኘ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ክህሎት ያለው የሰው ኃይል፣ ኢነርጂ፣ ኢንተርኔት እና የአይሲቲ ፓርኮችን ጨምሮ የመሰረተ ልማቶች አቅርቦት እንዲሁ የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ የገበያ አቅም እንዳላት አስረድተዋል።
ሪች ዲጂታል ምቹ እድሎቹን በመጠቀም በዘርፉ እንዲሰማራ ኮሚሽነሩ ጥሪ አቅርበዋል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽንና ቴክኖሎጂ ተቋም ሪች ዲጂታል (REACH Digital) ተወካዮች በበኩላቸው ተቋሙ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋዩን የማፍሰስ ጠንካራ ፍላጎት እንዳለው ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ለአይሲቲ ልማት አመቺ ምህዳር እንዳለ መናገራቸውን ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026