አዲስ አበባ፤ጥር 6/2017(ኢዜአ)፦የሞጆ ደረቅ ወደብ የማስፋፊያ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ 80 በመቶ ላይ መድረሱን የሞጆ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ደሳለኝ ጌታሁን ገለፁ።
የሞጆ ደረቅ ወደብን ወደ ሁለገብ የሎጅስቲክስ ማዕከል በመቀየር የወጪና ገቢ ንግድን ለማቀላጠፍ ከአመታት በፊት የማስፋፊያ ግንባታ መጀመሩ ይታወቃል።
ከተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን የተወጣጡ ባለሙያዎች የሞጆ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አፈፃፀምን ተመልክተዋል።
የሞጆ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ደሳለኝ ጌታሁን በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት፥ የሞጆ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ግንባታ በፍጥነት እየተከናወነ ነው።
የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ በ60 ሄክታር ላይ እየተገነባ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በዚህም የመሠረተ ልማት፣የኮንክሪት ንጣፍ፣ የአይሲቲ፣ የኤሌክትሮ መካኒካል፣ የአጥርና የመጋዘን ግንባታ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል።
በአጠቃላይ የመጀመሪያው ምዕራፍ ሥራ 80 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው፥ በቀጣይ አመት ፕሮጀክቱ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር አረጋግጠዋል።
የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ የወደቡን የማስተናገድ አቅም፣ ቅልጥፍና እና ተዛማጅ የሎጂስቲክስ አገልግሎቶች ደረጃ ከመሰረቱ እንደሚቀይረው አስረድተዋል፡፡
በተጨማሪም የኢትዮ-ጂቡቲን የንግድ ኮሪደር አቅም ታሳቢ በማድረግና የአገሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲሸከም ታስቦ ነው እየተገነባ ያለው።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025