አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፡- አዲስ ያስገባናቸው ድሮኖች ከከተማ ፀጥታ ቁጥጥር ባሻገር የቦርደር ሴኪዩሪቲን የኮንትሮባንድ እና ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን በቀላሉ መቆጣጠር የምንችልበትን ዕድል ይፈጥርልናል ሲሉ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ገለጹ።
ኮሚሽነር ጀነራሉ በዋናው መስሪያ ቤት የተደራጀውን የድሮን ፓይለት ማሰልጠኛ ማዕከል(UAV Simulation Training Center) መርቀው ስራ አስጀምረዋል፡፡
በዚሁ ወቅት ኮሚሽነር ጀነራሉ በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ ፖሊስ ውስጥ የተዋወቀው የድሮን ቴክኖሎጂ ማዕከል ወጣት የፖሊስ ኦፊሰሮቻችን የቴክኖሎጂ ስልጠና አግኝተው በፖሊስ ውስጥ የተሻለ የፖሊስ አገልግሎት ለመስጠት የተፈጠረ እንደሆነ ገልጸዋል።
አሁን ላይ በተቋሙ ያለው የድሮን አቅም በፖሊስ የወንጀል መከላከል ሰርቪላንስ እና የምርመራ ስራ ከፍተኛ እገዛ እንዳለውም ተናግረዋል፡፡
በፖሊስ ታሪክ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ፖሊስ በዘመኑ እንደዚህ አይነት ቴክኖሎጂዎችን ታጥቆ አያውቅም ያሉት ኮሚሽነር ጀነራሉ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በሪፎርሙ አሁን ላይ ከአፍሪካ አምስቱ ምርጥ የፖሊስ ተቋማት ውስጥ ለመግባት እያደረገ ያለውን ጥረት በሚያግዝና ለአፍሪካ ወንድሞቻችንም ልምድ እና ተሞክሮ ማስተላለፍ በሚያስችል መልኩ እየተደራጀ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡
በሪፎርሙ መንግስት ለፖሊስ በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት የሀገራችን ፖሊስ ዘመናዊ ትጥቆች እንዲኖሩትና ሰብዓዊ መብትን ባከበረ መልኩ የወንጀል መከላከል ስራዎቻችንን ለመስራት በሚያስችል አቅሙን እያሳደገ ነው ብለዋል፡፡
እንደአዲስ አበባ ያሉ ትላልቅ ከተሞችን ፓትሮል ለማድረግ የእግረኛ ፖሊስ ሠራዊትን ከድሮን ፓትሮል ጋር በማቀናጀት እና በማዋሀድ የወንጀል መከላከል ስራችንን እያቀላጠፍን የምንሰራበት እድል ከመፍጠር ባለፈ አድማዎች ሲያጋጥሙ በተደራጀና በጠንካራ ሠራዊታችንና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ታግዘን በቀላሉ ችግሮችን መቆጣጠር የሚያስችል አቅም ፈጥረናል ነው ያሉት፡፡
እንደ አፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ያሉ መድረኮች ሲኖሩ ለተወሰነ ጊዜ መንገዶችን ዘግቶ ቪአይፒዎችን ማስተናገድ የሚያስችል የራሱ የሆነ ኮማንድ ኮንትሮል ያለው ዘመናዊ Road block ተሸከርካሪም በዛሬው ዕለት ተመርቆ ስራ እንዲጀምር መደረጉን ከፌዴራል ፖሊስ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025