
አዳማ ፤ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት አመቱ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በስፋት እየተዘጋጀ በበጋ መስኖ ልማት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ።
የቢሮው ምክትል ኃላፊና የተፈጥሮ ሀብት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኤሊያስ ከድር ለኢዜአ እንደገለጹት የአፈር ለምነትን ለመጨመር የተፈጥሮ ማዳበሪያ የማይተካ ሚና አለው።
በክልሉ ባለፉት ሶስት ዓመታት የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት በስፋት እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው በአዘገጃጀትና አጠቃቀም ዙሪያ የአርሶ አደሮችን ግንዛቤ የማሳደግ ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል።
በዚህም በጀት ዓመቱ 250 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት የታቀደ ሲሆን በእስካሁኑ ሂደት ከ163 ሚሊዮን ሜትር ኩዩብ በላይ መደበኛና ቫርሚ ኮምፖስት ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ እየዋለ ይገኛል ብለዋል።
በክልሉ ባለፉት ዓመታት 287 የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጂያ ማዕከላት መገንባታቸውን ጠቁመው እስካሁን በተሰራው ስራ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በግብርና ምርትና ምርታማነት እድገት ላይ በጎ ተጽእኖ እያሳደረ መምጣቱን አስታውሰዋል።
በቢሮው የአፈር ለምነት ዳይሬክተር አቶ እሸቱ ለገሰ በበኩላቸው በክልሉ ከባለፈው ነሐሴ ወር አጋማሽ ጀምሮ የዘንድሮው የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይ ከመደበኛ ኮምፖስት በተጨማሪ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ቨርሚ ኮምፖስት እንዲሁም ከባዮጋስ ተረፈ ምርት የተፈጥሮ ማዳበሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በበጀት ዓመቱ የተዘጋጀው የተፈጥሮ ማዳበሪያ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሩ በክልሉ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ግብርና ምርትና ምርታማነት እድገት እንዲጨምር አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025