የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>በኦሮሚያ ክልል የተፈጥሮ ማዳበሪያ በስፋት እየተዘጋጀ በበጋ መስኖ ልማት ጥቅም ላይ እየዋለ ነው</p>

Jan 18, 2025

IDOPRESS

አዳማ ፤ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት አመቱ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በስፋት እየተዘጋጀ በበጋ መስኖ ልማት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ።

የቢሮው ምክትል ኃላፊና የተፈጥሮ ሀብት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኤሊያስ ከድር ለኢዜአ እንደገለጹት የአፈር ለምነትን ለመጨመር የተፈጥሮ ማዳበሪያ የማይተካ ሚና አለው።

በክልሉ ባለፉት ሶስት ዓመታት የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት በስፋት እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው በአዘገጃጀትና አጠቃቀም ዙሪያ የአርሶ አደሮችን ግንዛቤ የማሳደግ ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል።

በዚህም በጀት ዓመቱ 250 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት የታቀደ ሲሆን በእስካሁኑ ሂደት ከ163 ሚሊዮን ሜትር ኩዩብ በላይ መደበኛና ቫርሚ ኮምፖስት ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ እየዋለ ይገኛል ብለዋል።

በክልሉ ባለፉት ዓመታት 287 የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጂያ ማዕከላት መገንባታቸውን ጠቁመው እስካሁን በተሰራው ስራ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በግብርና ምርትና ምርታማነት እድገት ላይ በጎ ተጽእኖ እያሳደረ መምጣቱን አስታውሰዋል።

በቢሮው የአፈር ለምነት ዳይሬክተር አቶ እሸቱ ለገሰ በበኩላቸው በክልሉ ከባለፈው ነሐሴ ወር አጋማሽ ጀምሮ የዘንድሮው የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይ ከመደበኛ ኮምፖስት በተጨማሪ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ቨርሚ ኮምፖስት እንዲሁም ከባዮጋስ ተረፈ ምርት የተፈጥሮ ማዳበሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በበጀት ዓመቱ የተዘጋጀው የተፈጥሮ ማዳበሪያ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሩ በክልሉ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ግብርና ምርትና ምርታማነት እድገት እንዲጨምር አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025