የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>በኦሮሚያ ክልል የተፈጥሮ ማዳበሪያ በስፋት እየተዘጋጀ በበጋ መስኖ ልማት ጥቅም ላይ እየዋለ ነው</p>

Jan 18, 2025

IDOPRESS

አዳማ ፤ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት አመቱ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በስፋት እየተዘጋጀ በበጋ መስኖ ልማት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ።

የቢሮው ምክትል ኃላፊና የተፈጥሮ ሀብት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኤሊያስ ከድር ለኢዜአ እንደገለጹት የአፈር ለምነትን ለመጨመር የተፈጥሮ ማዳበሪያ የማይተካ ሚና አለው።

በክልሉ ባለፉት ሶስት ዓመታት የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት በስፋት እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው በአዘገጃጀትና አጠቃቀም ዙሪያ የአርሶ አደሮችን ግንዛቤ የማሳደግ ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል።

በዚህም በጀት ዓመቱ 250 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት የታቀደ ሲሆን በእስካሁኑ ሂደት ከ163 ሚሊዮን ሜትር ኩዩብ በላይ መደበኛና ቫርሚ ኮምፖስት ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ እየዋለ ይገኛል ብለዋል።

በክልሉ ባለፉት ዓመታት 287 የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጂያ ማዕከላት መገንባታቸውን ጠቁመው እስካሁን በተሰራው ስራ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በግብርና ምርትና ምርታማነት እድገት ላይ በጎ ተጽእኖ እያሳደረ መምጣቱን አስታውሰዋል።

በቢሮው የአፈር ለምነት ዳይሬክተር አቶ እሸቱ ለገሰ በበኩላቸው በክልሉ ከባለፈው ነሐሴ ወር አጋማሽ ጀምሮ የዘንድሮው የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይ ከመደበኛ ኮምፖስት በተጨማሪ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ቨርሚ ኮምፖስት እንዲሁም ከባዮጋስ ተረፈ ምርት የተፈጥሮ ማዳበሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በበጀት ዓመቱ የተዘጋጀው የተፈጥሮ ማዳበሪያ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሩ በክልሉ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ግብርና ምርትና ምርታማነት እድገት እንዲጨምር አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026