
ሮቤ፤ ጥር 9/2017 (ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ከ32 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ላይ ያባዛውን ምርጥ ዘር እየሰበሰበ መሆኑን አስታወቀ።
የኢንተርፕራይዙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የቦርድ አባላት በባሌ ቅርንጫፍ ሥር የሚገኙ የሮቤና ሲናና የእርሻ ማሳዎች የሰብል ስብሰባ ሂደት ያለበትን ደረጃ ተመልክቷል።
የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጫላ አበበ በወቅቱ እንደገለጹት ኢንተርፕራይዙ የምርጥ ዘር አቅርቦት ችግርን ለማቃለል የሚያግዙ ሥራዎችን እያካሄደ ነው።
በዚህም ኢንተርፕራይዙ ከ32 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ላይ ያባዛቸው የሰብል ዝርያዎች ከምርምር ተቋማት የተለቀቁ እንደሆኑ ጠቁመዋል።
እየተሰበሰቡ ከሚገኙት የሰብል ዝርያዎች መካከል የዋግ በሽታን በመቋቋም የተሻለ ምርት የሚሰጡ የስንዴና የቢራ ገብስ ዘር እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።

በተለያዩ ዞኖችና ስነ-ምህዳር ውስጥ ከሚባዙት የተለያዩ የሰብል አይነቶች ከ 870 ሺህ ኩንታል የሚበልጥ ምርጥ ዘር ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።
አቶ ጫላ እንዳሉት፣ የመስክ ምልከታው ዓላማ የሰብል ስብሰባ ሂደትን በመገምገም የዘር ብጠራና ስርጭትን በወቅቱና በሚፈለገው ደረጃ ተደራሽ ለማድረግ መሆኑን አመልክተዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026