
ሮቤ፤ ጥር 9/2017 (ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ከ32 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ላይ ያባዛውን ምርጥ ዘር እየሰበሰበ መሆኑን አስታወቀ።
የኢንተርፕራይዙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የቦርድ አባላት በባሌ ቅርንጫፍ ሥር የሚገኙ የሮቤና ሲናና የእርሻ ማሳዎች የሰብል ስብሰባ ሂደት ያለበትን ደረጃ ተመልክቷል።
የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጫላ አበበ በወቅቱ እንደገለጹት ኢንተርፕራይዙ የምርጥ ዘር አቅርቦት ችግርን ለማቃለል የሚያግዙ ሥራዎችን እያካሄደ ነው።
በዚህም ኢንተርፕራይዙ ከ32 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ላይ ያባዛቸው የሰብል ዝርያዎች ከምርምር ተቋማት የተለቀቁ እንደሆኑ ጠቁመዋል።
እየተሰበሰቡ ከሚገኙት የሰብል ዝርያዎች መካከል የዋግ በሽታን በመቋቋም የተሻለ ምርት የሚሰጡ የስንዴና የቢራ ገብስ ዘር እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።

በተለያዩ ዞኖችና ስነ-ምህዳር ውስጥ ከሚባዙት የተለያዩ የሰብል አይነቶች ከ 870 ሺህ ኩንታል የሚበልጥ ምርጥ ዘር ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።
አቶ ጫላ እንዳሉት፣ የመስክ ምልከታው ዓላማ የሰብል ስብሰባ ሂደትን በመገምገም የዘር ብጠራና ስርጭትን በወቅቱና በሚፈለገው ደረጃ ተደራሽ ለማድረግ መሆኑን አመልክተዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025