የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>ኢንተርፕራይዙ ከ32 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ላይ ያባዛውን ምርጥ ዘር እየሰበሰበ ነው </p>

Jan 18, 2025

IDOPRESS

ሮቤ፤ ጥር 9/2017 (ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ከ32 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ላይ ያባዛውን ምርጥ ዘር እየሰበሰበ መሆኑን አስታወቀ።

የኢንተርፕራይዙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የቦርድ አባላት በባሌ ቅርንጫፍ ሥር የሚገኙ የሮቤና ሲናና የእርሻ ማሳዎች የሰብል ስብሰባ ሂደት ያለበትን ደረጃ ተመልክቷል።

የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጫላ አበበ በወቅቱ እንደገለጹት ኢንተርፕራይዙ የምርጥ ዘር አቅርቦት ችግርን ለማቃለል የሚያግዙ ሥራዎችን እያካሄደ ነው።

በዚህም ኢንተርፕራይዙ ከ32 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ላይ ያባዛቸው የሰብል ዝርያዎች ከምርምር ተቋማት የተለቀቁ እንደሆኑ ጠቁመዋል።

እየተሰበሰቡ ከሚገኙት የሰብል ዝርያዎች መካከል የዋግ በሽታን በመቋቋም የተሻለ ምርት የሚሰጡ የስንዴና የቢራ ገብስ ዘር እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።


በተለያዩ ዞኖችና ስነ-ምህዳር ውስጥ ከሚባዙት የተለያዩ የሰብል አይነቶች ከ 870 ሺህ ኩንታል የሚበልጥ ምርጥ ዘር ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።

አቶ ጫላ እንዳሉት፣ የመስክ ምልከታው ዓላማ የሰብል ስብሰባ ሂደትን በመገምገም የዘር ብጠራና ስርጭትን በወቅቱና በሚፈለገው ደረጃ ተደራሽ ለማድረግ መሆኑን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025