የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>ኢንተርፕራይዙ ከ32 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ላይ ያባዛውን ምርጥ ዘር እየሰበሰበ ነው </p>

Jan 18, 2025

IDOPRESS

ሮቤ፤ ጥር 9/2017 (ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ከ32 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ላይ ያባዛውን ምርጥ ዘር እየሰበሰበ መሆኑን አስታወቀ።

የኢንተርፕራይዙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የቦርድ አባላት በባሌ ቅርንጫፍ ሥር የሚገኙ የሮቤና ሲናና የእርሻ ማሳዎች የሰብል ስብሰባ ሂደት ያለበትን ደረጃ ተመልክቷል።

የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጫላ አበበ በወቅቱ እንደገለጹት ኢንተርፕራይዙ የምርጥ ዘር አቅርቦት ችግርን ለማቃለል የሚያግዙ ሥራዎችን እያካሄደ ነው።

በዚህም ኢንተርፕራይዙ ከ32 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ላይ ያባዛቸው የሰብል ዝርያዎች ከምርምር ተቋማት የተለቀቁ እንደሆኑ ጠቁመዋል።

እየተሰበሰቡ ከሚገኙት የሰብል ዝርያዎች መካከል የዋግ በሽታን በመቋቋም የተሻለ ምርት የሚሰጡ የስንዴና የቢራ ገብስ ዘር እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።


በተለያዩ ዞኖችና ስነ-ምህዳር ውስጥ ከሚባዙት የተለያዩ የሰብል አይነቶች ከ 870 ሺህ ኩንታል የሚበልጥ ምርጥ ዘር ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።

አቶ ጫላ እንዳሉት፣ የመስክ ምልከታው ዓላማ የሰብል ስብሰባ ሂደትን በመገምገም የዘር ብጠራና ስርጭትን በወቅቱና በሚፈለገው ደረጃ ተደራሽ ለማድረግ መሆኑን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026