አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ የፋይዳ መታወቂያ የዲጂታል ማህበረሰብ መሰረተ ልማት ስራን ውጤታማ ለማድረግ ምቹ መደላድል መፍጠሩን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ገለጹ።
የቶኒ ብሌር ኢንስቲትዩት ያዘጋጀው የዲጂታል ፐብሊክ መሰረተ ልማት አውደ ጥናት በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
በአውደ ጥናቱ ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፣ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር፣ ከብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም፣ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ፣ ከኢትዮ ቴሌኮም እና ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ባለፉት አመታት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን በመተግበር በርካታ ውጤቶች ማስመዝገቧን ገልጸዋል።
አዲስ የተቀረጸው የዲጂታል መንግስት ስትራቴጂ አካል በሆነው የዲጂታል ማህበረሰብ መሰረተ ልማት አማካኝነት በትግበራ ላይ የሚገኘው ፋይዳ መታወቂያ ዘርፉን ለማሳደግ መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥር አመልክተዋል።
የቶኒ ብሌር ከፍተኛ አማካሪ እና የህንድ ኤሌክትሮኒክ፣ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እና ኢንተርፕረነርሺፕ ሚኒስትር ራጂቭ ቻንድራሴክሃር ህንድ በዲጂታል መሰረተ ልማት ያስመዘገበችውን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ውጤት አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።
ስትራቴጂካዊ እቅዶችን በመተግበር የዲጂታል መሰረተ ልማቶችን የማልማት ስራ ስኬት መመዝገቡን አመልክተዋል።
የቶኒ ብሌር ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ማለዳ ብስራት ኢንስቲትዩቱ የኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን እውን ለማድረግ ከመንግስት ጋር በቅርበት እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
ኢንስቲትዩቱ ለመንግስት የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስራዎች ድጋፍ እንደሚያደርግ መግለጻቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025