የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>በምዕራብ ጎንደር ዞን  የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ  ሥራ ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት እድገት  የጎላ አስተዋጽኦ አበርክቷል</p>

Jan 22, 2025

IDOPRESS

መተማ ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ጎንደር ዞን ባለፉት ዓመታት የተከናወነው የተቀናጀ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት እድገት የጎላ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በዞኑ መተማ ወረዳ ኩመር አፍጥጥ ቀበሌ የ2017 ዓመት የተፈጥሮ ሀብት ልማት ማስጀመሪያ መረሃ ግብር ዛሬ ተካሄዷል።

በዚህ ወቅት የዞኑ ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ጤናው ፈንታሁን እንደተናገሩት፤ ቀደም ሲል በተከናወነ የተቀናጀ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራዎች በደን ይዞታዎች ላይ ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ አስችሏል።


በተለይ ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ በርካታ ምርት ወደ ሌሎች አካባቢዎች ማቅረብ እንዳስቻለ አመልክተዋል።

በተለይም ማንጎ፣ ዘይቱን፣ ፓፓያ፣ ሙዝና ሌሎች አትክልትና ፍራፍሬዎች በተቀናጀ ተፋሰስ በማልማቱም የአካባቢው ማህበረሰብ ከምግብ ፍጆታ አልፎ ከምርት ሽያጭ ተጠቃሚ እንዲሆን አስችሏል።

በለሙ ተፋሰሶች የንብ ማነብ፣ የእንስሳት ማድለብ፣ በጎለበቱ ምንጮችና ወንዞች መስኖ ልማት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህ ዓመትም ያለፈውን ልምድና ተሞክሮ በማስፋት በ91 ተፋሰሶች ውስጥ አንድ ሺህ 500 ሄክታር በላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ለማከናወን ዛሬ ወደ ተግባር መገባቱን ተናግረዋል።

በዚህም ከ35 ሺህ በላይ ህዝብ ለማሳተፍ ታቅዶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩን ጠቅሰው፤ ለቀያሽ አርሶ አደሮች ስልጠናና የመስሪያ መሳሪያ ልየታ መከናወኑንም አስረድተዋል።


በሥራው እየተሰታፉ ካሉት መካከል የአካባቢው አርሶ አደር እሸቱ ይስማው በሰጡት አስተያየት፤ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ልማት ሥራው የተቦረቦሩ ስፍራዎች በማልማት ተጠቃሚ መሆን እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።

ከዚህ በፊት በለሙት ተፋሰሶች ለከብቶች መኖን ማልማት መጀመራቸውን ጠቅሰው፤ የተፋሰስ ልማት ስራው በየዓመቱ በጉጉት የሚጠብቁት መሆኑን አመልክተዋል።

ሌላኛው አርሶ አደር ከፋለ ይግዛው በበኩላቸው፤ በለሙት ተፋሰሶች ላይ አትክልትና ፍራፍሬ በመትከል መጠቀም መጀመራቸውን ተናግረዋል።

በተለይም ማንጎ፣ ፓፓያና ዘይቱን በማልማት ከፍጆታቸው አልፎ ለገበያ ማቅረብ መጀመራቸውን ጠቅሰው፤ በቀጣይም ሙዝና ሌሎች የቆላ ፍራፍሬዎችን ለማልማት መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል።

የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ሥራው ያስገኘው ጠቀሜታ ለማስቀጠልም እየተዘጋጁ መሆኑን አስታውቀዋል።

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቀደም ሲል በለሙ 42 ተፋሰሶች አንድ ሺህ 200 ለሚደርሱ ዜጎችን የስራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉም ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026