
አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2017(ኢዜአ)፦ኢዜአ በዲጂታል አማራጭ የአፍሪካ ድምጽ ለመሆን የጀመረው ስራ የአህጉሪቷን ጥቅሞች በጋራ ለማስጠበቅ እንደሚያግዝ የደቡብ ሱዳን ህዝቦች ንቅናቄ (SPLM) ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ ገለጹ።
የደቡብ ሱዳን ህዝቦች ንቅናቄ (SPLM) ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ በብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ለመሳተፍ ሰሞኑን አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወሳል።
ዋና ጸሃፊው በዛሬው እለትም የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አዲሱን የሚዲያ ኮምፕሌክስና የዲጂታል ሚዲያ መሰረተ ልማት ጎብኝተዋል።

ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ በዚሁ ወቅት አፍሪካን አቅሞች ለማስተሳሰርና የጋራ ትርክት ለመፍጠር ጠንካራ አፍሪካዊ ሚዲያ ሊኖር እንደሚገባም ተናግረዋል።
ከዚህ አኳያ ኢዜአ በዲጂታል አማራጭ የአፍሪካ ድምጽ ለመሆን “pulse of Africa’’ በሚል ስያሜ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች ተደራሽ ለመሆን የጀመራቸው ስራዎች የሚበረታቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ይህም አህጉሪቷ በልማትና በሌሎችም መስኮች ያላትን እምቅ አቅም ለማስተዋወቅ ሁነኛ መፍትሄ ይሆናል ብለዋል።

ከአፍሪካ ውጭ ያሉ መገናኛ ብዙሃን የአፍሪካዊያንን እውነት በማስተዋወቅ ረገድ ውስንነት እንደነበራቸው በመጥቀስ፤ ኢዜአ በዲጂታል አማራጭ የአፍሪካ ድምጽ ለመሆን የጀመረው ስራ አህጉሪቷን በሚገባት ልክ ለማስተዋወቅ ያግዛል ብለዋል።
ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ፤ የኢዜአ ሚዲያ ኮምፕሌክስ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ መደራጀቱን አድንቀው፤ ኢዜአ የአፍሪካ ሁነኛ ድምጽ ለመሆን በዲጂታል አማራጭ የጀመረውን ጉዞ ሁሉም አፍሪካዊ ሊደግፈው ይገባል ብለዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025