የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>ኢዜአ በዲጂታል አማራጭ የአፍሪካ ድምጽ ለመሆን የጀመረው ስራ የአህጉሪቷን ጥቅሞች በጋራ ለማስጠበቅ ያግዛል -ፒተር ላም ቦዝ</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2017(ኢዜአ)፦ኢዜአ በዲጂታል አማራጭ የአፍሪካ ድምጽ ለመሆን የጀመረው ስራ የአህጉሪቷን ጥቅሞች በጋራ ለማስጠበቅ እንደሚያግዝ የደቡብ ሱዳን ህዝቦች ንቅናቄ (SPLM) ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ ገለጹ።

የደቡብ ሱዳን ህዝቦች ንቅናቄ (SPLM) ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ በብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ለመሳተፍ ሰሞኑን አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወሳል።

ዋና ጸሃፊው በዛሬው እለትም የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አዲሱን የሚዲያ ኮምፕሌክስና የዲጂታል ሚዲያ መሰረተ ልማት ጎብኝተዋል።


ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ በዚሁ ወቅት አፍሪካን አቅሞች ለማስተሳሰርና የጋራ ትርክት ለመፍጠር ጠንካራ አፍሪካዊ ሚዲያ ሊኖር እንደሚገባም ተናግረዋል።

ከዚህ አኳያ ኢዜአ በዲጂታል አማራጭ የአፍሪካ ድምጽ ለመሆን “pulse of Africa’’ በሚል ስያሜ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች ተደራሽ ለመሆን የጀመራቸው ስራዎች የሚበረታቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ይህም አህጉሪቷ በልማትና በሌሎችም መስኮች ያላትን እምቅ አቅም ለማስተዋወቅ ሁነኛ መፍትሄ ይሆናል ብለዋል።


ከአፍሪካ ውጭ ያሉ መገናኛ ብዙሃን የአፍሪካዊያንን እውነት በማስተዋወቅ ረገድ ውስንነት እንደነበራቸው በመጥቀስ፤ ኢዜአ በዲጂታል አማራጭ የአፍሪካ ድምጽ ለመሆን የጀመረው ስራ አህጉሪቷን በሚገባት ልክ ለማስተዋወቅ ያግዛል ብለዋል።

ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ፤ የኢዜአ ሚዲያ ኮምፕሌክስ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ መደራጀቱን አድንቀው፤ ኢዜአ የአፍሪካ ሁነኛ ድምጽ ለመሆን በዲጂታል አማራጭ የጀመረውን ጉዞ ሁሉም አፍሪካዊ ሊደግፈው ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026