የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>ኢዜአ በዲጂታል አማራጭ የአፍሪካ ድምጽ ለመሆን የጀመረው ስራ የአህጉሪቷን ጥቅሞች በጋራ ለማስጠበቅ ያግዛል -ፒተር ላም ቦዝ</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2017(ኢዜአ)፦ኢዜአ በዲጂታል አማራጭ የአፍሪካ ድምጽ ለመሆን የጀመረው ስራ የአህጉሪቷን ጥቅሞች በጋራ ለማስጠበቅ እንደሚያግዝ የደቡብ ሱዳን ህዝቦች ንቅናቄ (SPLM) ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ ገለጹ።

የደቡብ ሱዳን ህዝቦች ንቅናቄ (SPLM) ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ በብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ለመሳተፍ ሰሞኑን አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወሳል።

ዋና ጸሃፊው በዛሬው እለትም የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አዲሱን የሚዲያ ኮምፕሌክስና የዲጂታል ሚዲያ መሰረተ ልማት ጎብኝተዋል።


ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ በዚሁ ወቅት አፍሪካን አቅሞች ለማስተሳሰርና የጋራ ትርክት ለመፍጠር ጠንካራ አፍሪካዊ ሚዲያ ሊኖር እንደሚገባም ተናግረዋል።

ከዚህ አኳያ ኢዜአ በዲጂታል አማራጭ የአፍሪካ ድምጽ ለመሆን “pulse of Africa’’ በሚል ስያሜ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች ተደራሽ ለመሆን የጀመራቸው ስራዎች የሚበረታቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ይህም አህጉሪቷ በልማትና በሌሎችም መስኮች ያላትን እምቅ አቅም ለማስተዋወቅ ሁነኛ መፍትሄ ይሆናል ብለዋል።


ከአፍሪካ ውጭ ያሉ መገናኛ ብዙሃን የአፍሪካዊያንን እውነት በማስተዋወቅ ረገድ ውስንነት እንደነበራቸው በመጥቀስ፤ ኢዜአ በዲጂታል አማራጭ የአፍሪካ ድምጽ ለመሆን የጀመረው ስራ አህጉሪቷን በሚገባት ልክ ለማስተዋወቅ ያግዛል ብለዋል።

ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ፤ የኢዜአ ሚዲያ ኮምፕሌክስ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ መደራጀቱን አድንቀው፤ ኢዜአ የአፍሪካ ሁነኛ ድምጽ ለመሆን በዲጂታል አማራጭ የጀመረውን ጉዞ ሁሉም አፍሪካዊ ሊደግፈው ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025