የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>ኢዜአ በዲጂታል አማራጭ የአፍሪካ ድምጽ ለመሆን የጀመረው ስራ የአህጉሪቷን ጥቅሞች በጋራ ለማስጠበቅ ያግዛል -ፒተር ላም ቦዝ</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2017(ኢዜአ)፦ኢዜአ በዲጂታል አማራጭ የአፍሪካ ድምጽ ለመሆን የጀመረው ስራ የአህጉሪቷን ጥቅሞች በጋራ ለማስጠበቅ እንደሚያግዝ የደቡብ ሱዳን ህዝቦች ንቅናቄ (SPLM) ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ ገለጹ።

የደቡብ ሱዳን ህዝቦች ንቅናቄ (SPLM) ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ በብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ለመሳተፍ ሰሞኑን አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወሳል።

ዋና ጸሃፊው በዛሬው እለትም የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አዲሱን የሚዲያ ኮምፕሌክስና የዲጂታል ሚዲያ መሰረተ ልማት ጎብኝተዋል።


ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ በዚሁ ወቅት አፍሪካን አቅሞች ለማስተሳሰርና የጋራ ትርክት ለመፍጠር ጠንካራ አፍሪካዊ ሚዲያ ሊኖር እንደሚገባም ተናግረዋል።

ከዚህ አኳያ ኢዜአ በዲጂታል አማራጭ የአፍሪካ ድምጽ ለመሆን “pulse of Africa’’ በሚል ስያሜ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች ተደራሽ ለመሆን የጀመራቸው ስራዎች የሚበረታቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ይህም አህጉሪቷ በልማትና በሌሎችም መስኮች ያላትን እምቅ አቅም ለማስተዋወቅ ሁነኛ መፍትሄ ይሆናል ብለዋል።


ከአፍሪካ ውጭ ያሉ መገናኛ ብዙሃን የአፍሪካዊያንን እውነት በማስተዋወቅ ረገድ ውስንነት እንደነበራቸው በመጥቀስ፤ ኢዜአ በዲጂታል አማራጭ የአፍሪካ ድምጽ ለመሆን የጀመረው ስራ አህጉሪቷን በሚገባት ልክ ለማስተዋወቅ ያግዛል ብለዋል።

ዋና ጸሃፊ ፒተር ላም ቦዝ፤ የኢዜአ ሚዲያ ኮምፕሌክስ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ መደራጀቱን አድንቀው፤ ኢዜአ የአፍሪካ ሁነኛ ድምጽ ለመሆን በዲጂታል አማራጭ የጀመረውን ጉዞ ሁሉም አፍሪካዊ ሊደግፈው ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026