
ወልዲያ፤ ጥር 28/2017 (ኢዜአ)፦ በወልዲያ-ቆቦ መንገድ የሚገኘው የአሚድ ወንዝ ብረት ድልድይ በመሰበሩ ድልድዩን በሌላ ለመተካት ጥረት እያደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስታወቀ።
በድልድዩ መሰበር ሳቢያ የተስተጓጎለውን የትራንስፖርት አገልግሎት ችግር በጊዜያዊ መፍትሄ ለመስጠት ተለዋጭ መተላለፊያ መንገድ መሰራቱን አስታውቋል።
በአስተዳደሩ የድልድዮችና ስትራክቸር ክፍል ዳይሬክተር ኢንጂነር ተክለስላሴ ንዳ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ትናንት ከሰዓት የአሚድ ወንዝ ብረት ድልድይ መሸከም ከሚችለው አቅም በላይ የጫነ ተሽከርካሪ ሲሻገር የብረት ድልድዩ ተደርምሷል።

በስፍራው የተፈጠረውን ትራንስፖርት አገልግሎት መስተጓጎል ለመፍታት አስተዳደሩ የግንባታ ማሽኖች ወደ ስፍራው ልኮ ተለዋጭ መንገድ በመስራት ጊዜያዊ መፍትሄ መስጠቱን ገልጸዋል።
በዚህም አነስተኛ ተሽከርካሪዎች በተለዋጭ መተላለፊያ መንገድ አገልግሎት እየሰጡ መሆን ገልጸዋል።
የብረት ድልድዩን በሌላ በመተካት ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠትም አስተዳደሩ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ መሆኑን ነው የተናገሩት።
ከወልዲያ ከተማ በ30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው የአሚድ ወንዝ ድልድይ 48 ሜትር ርዝመት ያለው የብረት ድልድዩ ነው።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025