የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>በወልዲያ-ቆቦ መንገድ የተሰበረውን የአሚድ ወንዝ የብረት ድልድይ በሌላ ለመተካት ጥረት እየተደረገ ነው- የመንገዶች አስተዳደር</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

ወልዲያ፤ ጥር 28/2017 (ኢዜአ)፦ በወልዲያ-ቆቦ መንገድ የሚገኘው የአሚድ ወንዝ ብረት ድልድይ በመሰበሩ ድልድዩን በሌላ ለመተካት ጥረት እያደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስታወቀ።

በድልድዩ መሰበር ሳቢያ የተስተጓጎለውን የትራንስፖርት አገልግሎት ችግር በጊዜያዊ መፍትሄ ለመስጠት ተለዋጭ መተላለፊያ መንገድ መሰራቱን አስታውቋል።

በአስተዳደሩ የድልድዮችና ስትራክቸር ክፍል ዳይሬክተር ኢንጂነር ተክለስላሴ ንዳ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ትናንት ከሰዓት የአሚድ ወንዝ ብረት ድልድይ መሸከም ከሚችለው አቅም በላይ የጫነ ተሽከርካሪ ሲሻገር የብረት ድልድዩ ተደርምሷል።


በስፍራው የተፈጠረውን ትራንስፖርት አገልግሎት መስተጓጎል ለመፍታት አስተዳደሩ የግንባታ ማሽኖች ወደ ስፍራው ልኮ ተለዋጭ መንገድ በመስራት ጊዜያዊ መፍትሄ መስጠቱን ገልጸዋል።

በዚህም አነስተኛ ተሽከርካሪዎች በተለዋጭ መተላለፊያ መንገድ አገልግሎት እየሰጡ መሆን ገልጸዋል።

የብረት ድልድዩን በሌላ በመተካት ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠትም አስተዳደሩ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ መሆኑን ነው የተናገሩት።

ከወልዲያ ከተማ በ30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው የአሚድ ወንዝ ድልድይ 48 ሜትር ርዝመት ያለው የብረት ድልድዩ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026