አዲስ አበባ፤ጥር 29/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት የለውጥ አመታትበቤት ልማት ዘርፍ በተደረገው የፖሊሲ ማሻሻያ አበረታች ውጤት መገኘቱን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከፖሊሲ ጥናት ኢኒስትቲዩት ጋር በመተባበር ባከናወነው የቤት ፋይናንስ ስርዓት ዝርጋታ የጥናት ማጎልበቻ ዙሪያ ያጠነጠነ መድረክ ዛሬ ተከናውኗል ፡፡
ስርዓቱ ፍትሃዊ የኢኮኖሚ እድገትን፣ በማጎልበት እና ድህነትን በመቀነስ ዜጎች ቋሚ የንብረት ባለቤት እንዲሆኑ ያስችላል ተብሏል፡፡
በዚሁ ወቅት የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ዴኤታ ሔለን ደበበ ባለፉት የለውጥ አመታት በቤት ልማት ዘርፍ በተደረገው የፖሊሲ ማሻሻያ አበረታች ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል፡፡
ነገር ግን በአጠቃላይ በከተሞች ካለው የቤት ፍላጎት አንጻር ብዙ መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
የህብረተሰቡን የመኖሪያ ቤት ፍላጎት ለሟሟላት ከቤት ፋይናንስ፣ ከአልሚዎች፣ ከመሬት ልማትና አቅርቦት ተቋማት፣ ከከተማ ፕላንና፣ ከዘርፉ ሙያተኞች ጋር ቅንጅት በመፍጠር በትብብር እየተሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡
በሀገሪቱ በቤት ፍላጎትና አቅርቦት መካከል ያለውን ክፍተት ለመሙላት ተግዳሮት ሆኖ የቆየው የቤት ፋይናንስ እጥረት መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በዚህ ረገድ የመኖሪያ ቤት ፍላጎቱን በመሙላት አቅርቦቱን ለማሳለጥ ራሱን የቻለ የቤት ፋይናንስና ምንጭ የአቅርቦት ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ይህን ተከትሎ ሚኒስቴሩ የህግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት ለውይይት ክፍት ማድረጉን ጠቁመዋል፡፡
የቤት ልማት የፋይናንስ ስርዓቱ በዋናነት የፋይናንስ ምንጮችን መለየት፣ የመኖሪያ ቤት ልማት ፋይናንስ የአቅርቦት ስርዓት አስተዳደርና አሰራር ዘዴን የሚያመላክት ነው ብለዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025