
አዲስ አበባ፤ጥር 29/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት የለውጥ አመታትበቤት ልማት ዘርፍ በተደረገው የፖሊሲ ማሻሻያ አበረታች ውጤት መገኘቱን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከፖሊሲ ጥናት ኢኒስትቲዩት ጋር በመተባበር ባከናወነው የቤት ፋይናንስ ስርዓት ዝርጋታ የጥናት ማጎልበቻ ዙሪያ ያጠነጠነ መድረክ ዛሬ ተከናውኗል ፡፡
ስርዓቱ ፍትሃዊ የኢኮኖሚ እድገትን፣ በማጎልበት እና ድህነትን በመቀነስ ዜጎች ቋሚ የንብረት ባለቤት እንዲሆኑ ያስችላል ተብሏል፡፡
በዚሁ ወቅት የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ዴኤታ ሔለን ደበበ ባለፉት የለውጥ አመታት በቤት ልማት ዘርፍ በተደረገው የፖሊሲ ማሻሻያ አበረታች ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል፡፡
ነገር ግን በአጠቃላይ በከተሞች ካለው የቤት ፍላጎት አንጻር ብዙ መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
የህብረተሰቡን የመኖሪያ ቤት ፍላጎት ለሟሟላት ከቤት ፋይናንስ፣ ከአልሚዎች፣ ከመሬት ልማትና አቅርቦት ተቋማት፣ ከከተማ ፕላንና፣ ከዘርፉ ሙያተኞች ጋር ቅንጅት በመፍጠር በትብብር እየተሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡
በሀገሪቱ በቤት ፍላጎትና አቅርቦት መካከል ያለውን ክፍተት ለመሙላት ተግዳሮት ሆኖ የቆየው የቤት ፋይናንስ እጥረት መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በዚህ ረገድ የመኖሪያ ቤት ፍላጎቱን በመሙላት አቅርቦቱን ለማሳለጥ ራሱን የቻለ የቤት ፋይናንስና ምንጭ የአቅርቦት ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ይህን ተከትሎ ሚኒስቴሩ የህግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት ለውይይት ክፍት ማድረጉን ጠቁመዋል፡፡
የቤት ልማት የፋይናንስ ስርዓቱ በዋናነት የፋይናንስ ምንጮችን መለየት፣ የመኖሪያ ቤት ልማት ፋይናንስ የአቅርቦት ስርዓት አስተዳደርና አሰራር ዘዴን የሚያመላክት ነው ብለዋል፡፡
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025