የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>ባለፉት የለውጥ አመታት በቤት ልማት ዘርፍ በተደረገው የፖሊሲ ማሻሻያ አበረታች ውጤት ተገኝቷል</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ጥር 29/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት የለውጥ አመታትበቤት ልማት ዘርፍ በተደረገው የፖሊሲ ማሻሻያ አበረታች ውጤት መገኘቱን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከፖሊሲ ጥናት ኢኒስትቲዩት ጋር በመተባበር ባከናወነው የቤት ፋይናንስ ስርዓት ዝርጋታ የጥናት ማጎልበቻ ዙሪያ ያጠነጠነ መድረክ ዛሬ ተከናውኗል ፡፡

ስርዓቱ ፍትሃዊ የኢኮኖሚ እድገትን፣ በማጎልበት እና ድህነትን በመቀነስ ዜጎች ቋሚ የንብረት ባለቤት እንዲሆኑ ያስችላል ተብሏል፡፡

በዚሁ ወቅት የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ዴኤታ ሔለን ደበበ ባለፉት የለውጥ አመታት በቤት ልማት ዘርፍ በተደረገው የፖሊሲ ማሻሻያ አበረታች ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል፡፡

ነገር ግን በአጠቃላይ በከተሞች ካለው የቤት ፍላጎት አንጻር ብዙ መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡

የህብረተሰቡን የመኖሪያ ቤት ፍላጎት ለሟሟላት ከቤት ፋይናንስ፣ ከአልሚዎች፣ ከመሬት ልማትና አቅርቦት ተቋማት፣ ከከተማ ፕላንና፣ ከዘርፉ ሙያተኞች ጋር ቅንጅት በመፍጠር በትብብር እየተሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡

በሀገሪቱ በቤት ፍላጎትና አቅርቦት መካከል ያለውን ክፍተት ለመሙላት ተግዳሮት ሆኖ የቆየው የቤት ፋይናንስ እጥረት መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በዚህ ረገድ የመኖሪያ ቤት ፍላጎቱን በመሙላት አቅርቦቱን ለማሳለጥ ራሱን የቻለ የቤት ፋይናንስና ምንጭ የአቅርቦት ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ይህን ተከትሎ ሚኒስቴሩ የህግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት ለውይይት ክፍት ማድረጉን ጠቁመዋል፡፡

የቤት ልማት የፋይናንስ ስርዓቱ በዋናነት የፋይናንስ ምንጮችን መለየት፣ የመኖሪያ ቤት ልማት ፋይናንስ የአቅርቦት ስርዓት አስተዳደርና አሰራር ዘዴን የሚያመላክት ነው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026