የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>በኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ ባለሀብቶች ሁለንተናዊ ድጋፍ ይደረጋል- ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ ጥር 29/2017 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በተለያዩ ኢንቨስትመንት አማራጮች ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረገው ሁለንተናዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለፁ።

የክልሉን የኢንቨስትመንት አማራጮች ከማስተዋወቅ ባለፈ ኢንቨስተሮቹ ምርትና አገልግሎታቸውን ለዕይታ ሚያቀርቡበት ለሁለት ቀናት የሚቆይ ዐውደ ርዕይና ፌስቲቫል ዛሬ በጋምቤላ ተጀምሯል።


የሁነቱ አካል የሆነ የፓናል ውይይት ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና ባለሃብቶች በተሳተፉበት እየተካሄደ ነው።

ርዕሰ መስተዳድሯ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በክልሉ ያሉትን ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ወደ ልማት ለማስገባት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።

በክልሉ ለኢንቨስትመንት ልማት የሚውል ሰፊ የተፈጥሮ ሃብት ቢኖሩም በተፈለገው ደረጃ ባለመልማቱ ህዝቡ ከዘርፉ በተገቢው ተጠቃሚ ሳይሆን እንደቆየ ተናግረዋል።

በክልሉ ያለውን የተፈጥሮ ሃብት በማልማት እንደ ክልል ብሎም እንደ አገር የታለውን የኢኮኖሚ እደገት እውን ለማድረግ ከባለሃብቱ የላቀ አበርክቶ ይጠብቃል ብለዋል።

በተለይም በግብርናው ዘርፍ የተሰማሩ ባለሃብቶች ከሚፈጥሩት የስራ እድል በተጨማሪ የአካባቢውን አርሶ አደሮች በቴክኖሎጂ በመደገፍ ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉና የምግብ ዋስተናቸውን እንዲያረጋገጡ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

ከለውጡ በፊት በክልሉ ሲስተዋሉ የነበሩት ያልተገቡ አሰራሮች በኢንቨስትመንት ፍሰት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደነበራቸው አስታውሰዋል።

የክልሉ መንግስት ችግሮችን በማስተካከል የኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲነቃቃ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።

በዚህም በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች በክልሉ ለሚሰማሩ አልሚ ባለሀብቶች የሚደረገው ሁለንተናዊ ድጋፍ ይቀጥላል ብለዋል።

ዐውደ ርዕይና ፌስቲቫሉ አዳዲስ ባለሀብቶችን ለመሳብና ነባር ባለሀብቶችን እንደሚያነቃቃ ጠቁመዋል።

የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሎው ኡቡፕ(ዶ/ር) በበኩላቸው የክልሉን ሰፊ የኢንቨስትመንት አቅም በማልማት ከዘርፉ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር ይሰራል ብለዋል።

ዐውደ ርዕዩ የክልሉን ጸጋዎች በማስተዋወቅ ክልሉን ዋነኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025