
ጋምቤላ፤ ጥር 29/2017 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በተለያዩ ኢንቨስትመንት አማራጮች ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረገው ሁለንተናዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለፁ።
የክልሉን የኢንቨስትመንት አማራጮች ከማስተዋወቅ ባለፈ ኢንቨስተሮቹ ምርትና አገልግሎታቸውን ለዕይታ ሚያቀርቡበት ለሁለት ቀናት የሚቆይ ዐውደ ርዕይና ፌስቲቫል ዛሬ በጋምቤላ ተጀምሯል።

የሁነቱ አካል የሆነ የፓናል ውይይት ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና ባለሃብቶች በተሳተፉበት እየተካሄደ ነው።
ርዕሰ መስተዳድሯ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በክልሉ ያሉትን ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ወደ ልማት ለማስገባት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
በክልሉ ለኢንቨስትመንት ልማት የሚውል ሰፊ የተፈጥሮ ሃብት ቢኖሩም በተፈለገው ደረጃ ባለመልማቱ ህዝቡ ከዘርፉ በተገቢው ተጠቃሚ ሳይሆን እንደቆየ ተናግረዋል።
በክልሉ ያለውን የተፈጥሮ ሃብት በማልማት እንደ ክልል ብሎም እንደ አገር የታለውን የኢኮኖሚ እደገት እውን ለማድረግ ከባለሃብቱ የላቀ አበርክቶ ይጠብቃል ብለዋል።
በተለይም በግብርናው ዘርፍ የተሰማሩ ባለሃብቶች ከሚፈጥሩት የስራ እድል በተጨማሪ የአካባቢውን አርሶ አደሮች በቴክኖሎጂ በመደገፍ ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉና የምግብ ዋስተናቸውን እንዲያረጋገጡ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
ከለውጡ በፊት በክልሉ ሲስተዋሉ የነበሩት ያልተገቡ አሰራሮች በኢንቨስትመንት ፍሰት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደነበራቸው አስታውሰዋል።
የክልሉ መንግስት ችግሮችን በማስተካከል የኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲነቃቃ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።
በዚህም በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች በክልሉ ለሚሰማሩ አልሚ ባለሀብቶች የሚደረገው ሁለንተናዊ ድጋፍ ይቀጥላል ብለዋል።
ዐውደ ርዕይና ፌስቲቫሉ አዳዲስ ባለሀብቶችን ለመሳብና ነባር ባለሀብቶችን እንደሚያነቃቃ ጠቁመዋል።
የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሎው ኡቡፕ(ዶ/ር) በበኩላቸው የክልሉን ሰፊ የኢንቨስትመንት አቅም በማልማት ከዘርፉ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር ይሰራል ብለዋል።
ዐውደ ርዕዩ የክልሉን ጸጋዎች በማስተዋወቅ ክልሉን ዋነኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ገልጸዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026