የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>በኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ ባለሀብቶች ሁለንተናዊ ድጋፍ ይደረጋል- ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ ጥር 29/2017 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በተለያዩ ኢንቨስትመንት አማራጮች ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረገው ሁለንተናዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለፁ።

የክልሉን የኢንቨስትመንት አማራጮች ከማስተዋወቅ ባለፈ ኢንቨስተሮቹ ምርትና አገልግሎታቸውን ለዕይታ ሚያቀርቡበት ለሁለት ቀናት የሚቆይ ዐውደ ርዕይና ፌስቲቫል ዛሬ በጋምቤላ ተጀምሯል።


የሁነቱ አካል የሆነ የፓናል ውይይት ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና ባለሃብቶች በተሳተፉበት እየተካሄደ ነው።

ርዕሰ መስተዳድሯ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በክልሉ ያሉትን ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ወደ ልማት ለማስገባት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።

በክልሉ ለኢንቨስትመንት ልማት የሚውል ሰፊ የተፈጥሮ ሃብት ቢኖሩም በተፈለገው ደረጃ ባለመልማቱ ህዝቡ ከዘርፉ በተገቢው ተጠቃሚ ሳይሆን እንደቆየ ተናግረዋል።

በክልሉ ያለውን የተፈጥሮ ሃብት በማልማት እንደ ክልል ብሎም እንደ አገር የታለውን የኢኮኖሚ እደገት እውን ለማድረግ ከባለሃብቱ የላቀ አበርክቶ ይጠብቃል ብለዋል።

በተለይም በግብርናው ዘርፍ የተሰማሩ ባለሃብቶች ከሚፈጥሩት የስራ እድል በተጨማሪ የአካባቢውን አርሶ አደሮች በቴክኖሎጂ በመደገፍ ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉና የምግብ ዋስተናቸውን እንዲያረጋገጡ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

ከለውጡ በፊት በክልሉ ሲስተዋሉ የነበሩት ያልተገቡ አሰራሮች በኢንቨስትመንት ፍሰት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደነበራቸው አስታውሰዋል።

የክልሉ መንግስት ችግሮችን በማስተካከል የኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲነቃቃ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።

በዚህም በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች በክልሉ ለሚሰማሩ አልሚ ባለሀብቶች የሚደረገው ሁለንተናዊ ድጋፍ ይቀጥላል ብለዋል።

ዐውደ ርዕይና ፌስቲቫሉ አዳዲስ ባለሀብቶችን ለመሳብና ነባር ባለሀብቶችን እንደሚያነቃቃ ጠቁመዋል።

የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሎው ኡቡፕ(ዶ/ር) በበኩላቸው የክልሉን ሰፊ የኢንቨስትመንት አቅም በማልማት ከዘርፉ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር ይሰራል ብለዋል።

ዐውደ ርዕዩ የክልሉን ጸጋዎች በማስተዋወቅ ክልሉን ዋነኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026