አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በግምገማችን ባለፉት ስድስት ወራት መገንባት የጀመርነውን ጠንካራ የስራ ባህል የአመራር ቁርጠኝነትንና ቅንጅትን በማጠናከር እንዲሁም የገቢ አሰባሰብን በማሳደግ በርካታ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት በጥራት አጠናቀን ለህዝባችን ግልጋሎት ክፍት አድርገናል ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
የሀገርን ክብር በሚመጥን መልኩ ውብ፣ ጽዱ እና ለመኖር ምቹ ለማድረግ የጀመርነው የኮሪደር ልማት ስራ አዲስ አበባን አለም አቀፍ የስበት ማዕከል ከማድረግ በተጨማሪ ለነዋሪዎቻችን ምቹ የመኖሪያ አካባቢ እና ሰፊ የስራ እድል የፈጠሩ፣ አገልግሎትን የሚያሳልጡ ተግባሮች ተከናዉነዋል፣ የተቀሩትንም በቀሪ ወራት በፍጥነት የምናጠናቅቅ ይሆናል ነው ያሉት።
በቀጣይም የአፈፃፀም ዉስንነትን በማስተካከል፣ ማዘመን የጀመርነዉን አገልግሎት አሰጣጥን በማጠናከር ቀልጣፋ እና ፈጣን እንዲሁም በቴክኖሎጂ የተደገፈ ተደራሽ በማድረግ፣ ብልሹ አሰራር እና ጉቦኝነትን በመታገል እንዲሁም የገቢ አሰባሰብ እና ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር የተጀመሩ ስራዎችን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ በትኩረት የምንሰራ ይሆናል ሲሉ ገልጸዋል።
ከከተማችን ነዋሪዎች ጋር በመተባበር ድክመቶቻችንን ከነመንስዔዎቻቸው ተነቅሰው እንዲታረሙ እያደረግን ለላቀ ውጤታማነት መትጋታችንን የምንቀጥል ይሆናል ብለዋል በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025