የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>የንግድ ትርኢትና በዛር በደብረ ብርሃን ከተማ ተከፈተ</p>

Feb 11, 2025

IDOPRESS

ደብረብርሀን ፤ የካቲት 3/2017 (ኢዜአ) ፡- አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ለማቅረብ የተዘጋጀ የንግድ ትርኢትና በዛር በደብረ ብርሃን ከተማ ተከፈተ።

በዝግጅቱ ከ150 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ በጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት የተደራጁ ወጣቶች መሳተፋቸው ተገልጿል።

የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በመክፈቻው ላይ እንደተናገሩት፤ የንግድ ትርኢትና ባዛሩ አምራቹን ከሸማቹ ማህበረሰብ ጋር በቀጥታ በማገናኘት የዋጋ ጭማሪን ለመቀነስ ያለመ ነው።

የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በብዛትና በጥራት በማቅረብ ህብረተሰቡ የመግዛት አማራጩ እንዲሰፋ የሚያስችል መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የደብረ ብርሃን ንግድ መምሪያ ሀላፊ ወይዘሮ ይርጋለም ምስጋናው በበኩላቸው፤ የንግድ ትርኢትና ባዛሩ በግብርናና በኢንዱስትሪ ምርቶች ላይ የሚስተዋለውን ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ለመከላከል የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል።


በዚህም ከ150 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ በጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት የተደራጁ ወጣቶች መሳተፋቸውን አስታውቀዋል።

ዝግጅቱ ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የመደጋገፍና የመረዳዳት ባህልን ለማጎልበት እንደሚረዳ የገለጹት የደብረ ብርሃን ንግድና ዘርፍ ምክር ቤት ፕሬዚደንት አቶ አማረ ገብረ ዮሀንስ ናቸው።

በተጨማሪም በአንዳንድ ህገ ወጥ ነጋዴዎች የሚስተዋለውን ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ለመከላከል እንደሚያግዝ ጠቁመው ፤ የምክር ቤቱን ህንጻ ለማስገንባት በሚደረገው ጥረት ሁሉም አካል እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።


የወደራ የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበራት ዩኒዬን የግብርና ምርቶች የግብይት ክፍል ሃላፊ አቶ ወርቁ ባዘዘው እንዳሉት፤ ዩኒዬኑ ከአምስት ሺህ ኩንታል በላይ የጤፍ፣ ማሽላና የተለያዩ የጥራጥሬ ሰብሎችን በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቧል።

የንግድ ትርኢትና ባዛሩ ለተከታታይ አስራ አምስት ቀናት እንደሚቆይ ከከተማ አስተዳደሩ ንግድ መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025