ደብረብርሀን ፤ የካቲት 3/2017 (ኢዜአ) ፡- አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ለማቅረብ የተዘጋጀ የንግድ ትርኢትና በዛር በደብረ ብርሃን ከተማ ተከፈተ።
በዝግጅቱ ከ150 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ በጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት የተደራጁ ወጣቶች መሳተፋቸው ተገልጿል።
የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በመክፈቻው ላይ እንደተናገሩት፤ የንግድ ትርኢትና ባዛሩ አምራቹን ከሸማቹ ማህበረሰብ ጋር በቀጥታ በማገናኘት የዋጋ ጭማሪን ለመቀነስ ያለመ ነው።
የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በብዛትና በጥራት በማቅረብ ህብረተሰቡ የመግዛት አማራጩ እንዲሰፋ የሚያስችል መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የደብረ ብርሃን ንግድ መምሪያ ሀላፊ ወይዘሮ ይርጋለም ምስጋናው በበኩላቸው፤ የንግድ ትርኢትና ባዛሩ በግብርናና በኢንዱስትሪ ምርቶች ላይ የሚስተዋለውን ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ለመከላከል የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም ከ150 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ በጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት የተደራጁ ወጣቶች መሳተፋቸውን አስታውቀዋል።
ዝግጅቱ ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የመደጋገፍና የመረዳዳት ባህልን ለማጎልበት እንደሚረዳ የገለጹት የደብረ ብርሃን ንግድና ዘርፍ ምክር ቤት ፕሬዚደንት አቶ አማረ ገብረ ዮሀንስ ናቸው።
በተጨማሪም በአንዳንድ ህገ ወጥ ነጋዴዎች የሚስተዋለውን ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ለመከላከል እንደሚያግዝ ጠቁመው ፤ የምክር ቤቱን ህንጻ ለማስገንባት በሚደረገው ጥረት ሁሉም አካል እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።
የወደራ የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበራት ዩኒዬን የግብርና ምርቶች የግብይት ክፍል ሃላፊ አቶ ወርቁ ባዘዘው እንዳሉት፤ ዩኒዬኑ ከአምስት ሺህ ኩንታል በላይ የጤፍ፣ ማሽላና የተለያዩ የጥራጥሬ ሰብሎችን በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቧል።
የንግድ ትርኢትና ባዛሩ ለተከታታይ አስራ አምስት ቀናት እንደሚቆይ ከከተማ አስተዳደሩ ንግድ መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025