
ደብረብርሀን ፤ የካቲት 3/2017 (ኢዜአ) ፡- አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ለማቅረብ የተዘጋጀ የንግድ ትርኢትና በዛር በደብረ ብርሃን ከተማ ተከፈተ።
በዝግጅቱ ከ150 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ በጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት የተደራጁ ወጣቶች መሳተፋቸው ተገልጿል።
የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በመክፈቻው ላይ እንደተናገሩት፤ የንግድ ትርኢትና ባዛሩ አምራቹን ከሸማቹ ማህበረሰብ ጋር በቀጥታ በማገናኘት የዋጋ ጭማሪን ለመቀነስ ያለመ ነው።
የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በብዛትና በጥራት በማቅረብ ህብረተሰቡ የመግዛት አማራጩ እንዲሰፋ የሚያስችል መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የደብረ ብርሃን ንግድ መምሪያ ሀላፊ ወይዘሮ ይርጋለም ምስጋናው በበኩላቸው፤ የንግድ ትርኢትና ባዛሩ በግብርናና በኢንዱስትሪ ምርቶች ላይ የሚስተዋለውን ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ለመከላከል የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም ከ150 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ በጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት የተደራጁ ወጣቶች መሳተፋቸውን አስታውቀዋል።
ዝግጅቱ ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የመደጋገፍና የመረዳዳት ባህልን ለማጎልበት እንደሚረዳ የገለጹት የደብረ ብርሃን ንግድና ዘርፍ ምክር ቤት ፕሬዚደንት አቶ አማረ ገብረ ዮሀንስ ናቸው።
በተጨማሪም በአንዳንድ ህገ ወጥ ነጋዴዎች የሚስተዋለውን ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ለመከላከል እንደሚያግዝ ጠቁመው ፤ የምክር ቤቱን ህንጻ ለማስገንባት በሚደረገው ጥረት ሁሉም አካል እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

የወደራ የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበራት ዩኒዬን የግብርና ምርቶች የግብይት ክፍል ሃላፊ አቶ ወርቁ ባዘዘው እንዳሉት፤ ዩኒዬኑ ከአምስት ሺህ ኩንታል በላይ የጤፍ፣ ማሽላና የተለያዩ የጥራጥሬ ሰብሎችን በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቧል።
የንግድ ትርኢትና ባዛሩ ለተከታታይ አስራ አምስት ቀናት እንደሚቆይ ከከተማ አስተዳደሩ ንግድ መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026