
ደብረብርሀን ፤ የካቲት 3/2017 (ኢዜአ) ፡- አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ለማቅረብ የተዘጋጀ የንግድ ትርኢትና በዛር በደብረ ብርሃን ከተማ ተከፈተ።
በዝግጅቱ ከ150 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ በጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት የተደራጁ ወጣቶች መሳተፋቸው ተገልጿል።
የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በመክፈቻው ላይ እንደተናገሩት፤ የንግድ ትርኢትና ባዛሩ አምራቹን ከሸማቹ ማህበረሰብ ጋር በቀጥታ በማገናኘት የዋጋ ጭማሪን ለመቀነስ ያለመ ነው።
የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በብዛትና በጥራት በማቅረብ ህብረተሰቡ የመግዛት አማራጩ እንዲሰፋ የሚያስችል መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የደብረ ብርሃን ንግድ መምሪያ ሀላፊ ወይዘሮ ይርጋለም ምስጋናው በበኩላቸው፤ የንግድ ትርኢትና ባዛሩ በግብርናና በኢንዱስትሪ ምርቶች ላይ የሚስተዋለውን ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ለመከላከል የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም ከ150 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ በጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት የተደራጁ ወጣቶች መሳተፋቸውን አስታውቀዋል።
ዝግጅቱ ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የመደጋገፍና የመረዳዳት ባህልን ለማጎልበት እንደሚረዳ የገለጹት የደብረ ብርሃን ንግድና ዘርፍ ምክር ቤት ፕሬዚደንት አቶ አማረ ገብረ ዮሀንስ ናቸው።
በተጨማሪም በአንዳንድ ህገ ወጥ ነጋዴዎች የሚስተዋለውን ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ለመከላከል እንደሚያግዝ ጠቁመው ፤ የምክር ቤቱን ህንጻ ለማስገንባት በሚደረገው ጥረት ሁሉም አካል እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

የወደራ የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበራት ዩኒዬን የግብርና ምርቶች የግብይት ክፍል ሃላፊ አቶ ወርቁ ባዘዘው እንዳሉት፤ ዩኒዬኑ ከአምስት ሺህ ኩንታል በላይ የጤፍ፣ ማሽላና የተለያዩ የጥራጥሬ ሰብሎችን በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቧል።
የንግድ ትርኢትና ባዛሩ ለተከታታይ አስራ አምስት ቀናት እንደሚቆይ ከከተማ አስተዳደሩ ንግድ መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026