አርባ ምንጭ፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይት በሚሳተፉ አካላት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ ባውዲ ገለጹ።
በክልሉ ከ49 ሚሊዮን 552 ሺህ ብር በላይ ግምት ያለው ህገ-ወጥ ነዳጅ መያዙም ተመልክቷል።
በነዳጅ ምርቶች አዋጅ፣ በአቅርቦትና ስርጭት ላይ ያተኮረ መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ በተካሄደበት ወቅት አቶ አለማየሁ እንዳመለከቱት፤ በክልሉ ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይት ችግር እየፈጠረ ነው።
ህብረተሰቡን እየጎዱና ለመልካም አስተዳደር ችግር እያጋለጡ ያሉ የነዳጅ ማደያዎችን በመለየት ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ የመውሰዱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ገሌቦ ጎልቶሞ በበኩላቸው፤ መንግስት በከፍተኛ ድጎማ ነዳጅን ከውጭ ቢያስገባም ለዘርፉ ቅርበት ያላቸው አካላት የግብይት ሰንሰለቱን በማዛባት ተግዳሮት እየፈጠሩ ይገኛሉ ብለዋል።
በበጀት ዓመቱ በህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይት ላይ ተሰማርተው ህዝብን ለችግር እያጋለጡ ያሉትን አካላት ለመከላከል በተደረገው ጥረት ከ49 ሚሊዮን 552 ሺህ ብር በላይ ግምት ያለው ህገ-ወጥ ነዳጅ መያዙን ጠቅሰዋል።
በህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይት ላይ ሲንቀሳቀሱ በተገኙ አካላት ላይ የማያዳግም እርምጃ ለመውሰድ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ይሠራል ብለዋል።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍሰሃ ጋረደው በበኩላቸው፤ ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትና የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን ለመከላከል በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።
ለአንድ ቀን በተዘጋጀው መድረክ የክልሉና የዞን የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች፣ የንግድና ገበያ ልማት ባለሙያዎች፣ የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች፣ የፀጥታ አካላትና ሌሎች የተሳተፉ ሲሆን፤ በአዲሱ የነዳጅ ግብይት አዋጅ ላይም ግንዛቤ የማስጨበጫ መርሃ ግብር ተካሄዷል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025