የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትን የመቆጣጠሩ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል</p>

Feb 14, 2025

IDOPRESS

አርባ ምንጭ፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይት በሚሳተፉ አካላት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ ባውዲ ገለጹ።

በክልሉ ከ49 ሚሊዮን 552 ሺህ ብር በላይ ግምት ያለው ህገ-ወጥ ነዳጅ መያዙም ተመልክቷል።

በነዳጅ ምርቶች አዋጅ፣ በአቅርቦትና ስርጭት ላይ ያተኮረ መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ በተካሄደበት ወቅት አቶ አለማየሁ እንዳመለከቱት፤ በክልሉ ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይት ችግር እየፈጠረ ነው።


ህብረተሰቡን እየጎዱና ለመልካም አስተዳደር ችግር እያጋለጡ ያሉ የነዳጅ ማደያዎችን በመለየት ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ የመውሰዱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ገሌቦ ጎልቶሞ በበኩላቸው፤ መንግስት በከፍተኛ ድጎማ ነዳጅን ከውጭ ቢያስገባም ለዘርፉ ቅርበት ያላቸው አካላት የግብይት ሰንሰለቱን በማዛባት ተግዳሮት እየፈጠሩ ይገኛሉ ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ በህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይት ላይ ተሰማርተው ህዝብን ለችግር እያጋለጡ ያሉትን አካላት ለመከላከል በተደረገው ጥረት ከ49 ሚሊዮን 552 ሺህ ብር በላይ ግምት ያለው ህገ-ወጥ ነዳጅ መያዙን ጠቅሰዋል።

በህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይት ላይ ሲንቀሳቀሱ በተገኙ አካላት ላይ የማያዳግም እርምጃ ለመውሰድ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ይሠራል ብለዋል።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍሰሃ ጋረደው በበኩላቸው፤ ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትና የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን ለመከላከል በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።

ለአንድ ቀን በተዘጋጀው መድረክ የክልሉና የዞን የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች፣ የንግድና ገበያ ልማት ባለሙያዎች፣ የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች፣ የፀጥታ አካላትና ሌሎች የተሳተፉ ሲሆን፤ በአዲሱ የነዳጅ ግብይት አዋጅ ላይም ግንዛቤ የማስጨበጫ መርሃ ግብር ተካሄዷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025