
አዲስ አበባ፤ የካቲት 9/2017(ኢዜአ)፡- በአፍሪካ ሀገራት መካከል የንግድ ትስስርን ለማሳለጥ የመሰረተ ልማት ግንባታን ማጠናከር እንደሚገባ የፓን አፍሪካ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ዚ ቻሩሚቢራ ተናገሩ፡፡
በ38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የፓን አፍሪካ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ዚ ቻሩሚቢራ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ጉባኤው በወሳኝ ጉዳዮች ላይ መምከሩን ተናግረዋል፡፡
በተለይ የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጣናን እውን በማድረግ የአህጉሪቱን ህዝቦች ተጠቃሚ ማድረግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ መወያየቱ ወሳኝ እና አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል፡፡
የአፍሪካ ሀገራት የንግድ ልውውጥ መጠናከር የአህጉሪቱን ኢኮኖሚ ስለሚያሳድግ ጉዳዩ ትኩረት ማግኘቱ ተገቢ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
በአፍሪካ ሀገራት መካከል የሚደረግ የንግድ ልውውጥ ከፍተኛ እድገት የሚያመጣ መሆኑን አመልክተው፤ በመሰረተ ልማት ግንባታ ላይ ይበልጥ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
የንግድ ልውውጥ የሰዎችን ነጻ ዝውውር የሚፈልግ መሆኑን አመልክተው፤ ለስኬታማነቱ የሀገራት መሪዎች በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸው ተናግርዋል።
ለአንድ ሀገር እድገት ሰላም ወሳኝ መሆኑን ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ የአፍሪካ ሀገራት ለሰላም ግንባታና ውጤታማነት መስራት እንደሚገባም አስታውቀዋል፡፡
የአፍሪካ ሀገራት ሰላምንና ደህንነትን ለማረጋገጥ ትልቅ ሚና የሚኖረው ስትራቴጂ መዘርጋት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ "የማካካሻ ፍትሕ ለአፍሪካውያንና ዘርዓ-አፍሪካውያን" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026