የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>በአፍሪካ የንግድ ትስስርን ለማሳለጥ የመሰረተ ልማት ግንባታን ማጠናከር ይገባል - የፓን አፍሪካ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ዚ ቻሩሚቢራ</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 9/2017(ኢዜአ)፡- በአፍሪካ ሀገራት መካከል የንግድ ትስስርን ለማሳለጥ የመሰረተ ልማት ግንባታን ማጠናከር እንደሚገባ የፓን አፍሪካ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ዚ ቻሩሚቢራ ተናገሩ፡፡

በ38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የፓን አፍሪካ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ዚ ቻሩሚቢራ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ጉባኤው በወሳኝ ጉዳዮች ላይ መምከሩን ተናግረዋል፡፡

በተለይ የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጣናን እውን በማድረግ የአህጉሪቱን ህዝቦች ተጠቃሚ ማድረግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ መወያየቱ ወሳኝ እና አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል፡፡

የአፍሪካ ሀገራት የንግድ ልውውጥ መጠናከር የአህጉሪቱን ኢኮኖሚ ስለሚያሳድግ ጉዳዩ ትኩረት ማግኘቱ ተገቢ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

በአፍሪካ ሀገራት መካከል የሚደረግ የንግድ ልውውጥ ከፍተኛ እድገት የሚያመጣ መሆኑን አመልክተው፤ በመሰረተ ልማት ግንባታ ላይ ይበልጥ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

የንግድ ልውውጥ የሰዎችን ነጻ ዝውውር የሚፈልግ መሆኑን አመልክተው፤ ለስኬታማነቱ የሀገራት መሪዎች በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸው ተናግርዋል።

ለአንድ ሀገር እድገት ሰላም ወሳኝ መሆኑን ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ የአፍሪካ ሀገራት ለሰላም ግንባታና ውጤታማነት መስራት እንደሚገባም አስታውቀዋል፡፡

የአፍሪካ ሀገራት ሰላምንና ደህንነትን ለማረጋገጥ ትልቅ ሚና የሚኖረው ስትራቴጂ መዘርጋት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ "የማካካሻ ፍትሕ ለአፍሪካውያንና ዘርዓ-አፍሪካውያን" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026