
አዲስ አበባ፤ የካቲት 9/2017(ኢዜአ)፡- በአፍሪካ ሀገራት መካከል የንግድ ትስስርን ለማሳለጥ የመሰረተ ልማት ግንባታን ማጠናከር እንደሚገባ የፓን አፍሪካ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ዚ ቻሩሚቢራ ተናገሩ፡፡
በ38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የፓን አፍሪካ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ዚ ቻሩሚቢራ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ጉባኤው በወሳኝ ጉዳዮች ላይ መምከሩን ተናግረዋል፡፡
በተለይ የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጣናን እውን በማድረግ የአህጉሪቱን ህዝቦች ተጠቃሚ ማድረግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ መወያየቱ ወሳኝ እና አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል፡፡
የአፍሪካ ሀገራት የንግድ ልውውጥ መጠናከር የአህጉሪቱን ኢኮኖሚ ስለሚያሳድግ ጉዳዩ ትኩረት ማግኘቱ ተገቢ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
በአፍሪካ ሀገራት መካከል የሚደረግ የንግድ ልውውጥ ከፍተኛ እድገት የሚያመጣ መሆኑን አመልክተው፤ በመሰረተ ልማት ግንባታ ላይ ይበልጥ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
የንግድ ልውውጥ የሰዎችን ነጻ ዝውውር የሚፈልግ መሆኑን አመልክተው፤ ለስኬታማነቱ የሀገራት መሪዎች በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸው ተናግርዋል።
ለአንድ ሀገር እድገት ሰላም ወሳኝ መሆኑን ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ የአፍሪካ ሀገራት ለሰላም ግንባታና ውጤታማነት መስራት እንደሚገባም አስታውቀዋል፡፡
የአፍሪካ ሀገራት ሰላምንና ደህንነትን ለማረጋገጥ ትልቅ ሚና የሚኖረው ስትራቴጂ መዘርጋት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ "የማካካሻ ፍትሕ ለአፍሪካውያንና ዘርዓ-አፍሪካውያን" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026