ጅማ፤የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮ ቴሌኮም በጅማ ከተማ የአምስተኛውን ትውልድ የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት ዛሬ አስጀመረ።
በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩና የኩባንያው ከፍተኛ አመራር አባላት እንዲሁም የጅማ ከተማና የጅማ ዞን አመራሮችና የአገልግሎቱ ደንበኞች ተገኝተዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ፍሬህይወት ታምሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ኩባንያው አገልግሎት አሰጣጡን በማሻሻል ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን የማድረግ ጉዞ ላይ ነው።
የአምስተኛው ትውልድ ኔትወርክ አገልግሎት የዓለማችን ፈጣንና ቀልጣፋ የኔትወርክ አገልግሎት መሆኑን አንስተው አዲስ አበባን ጨምሮ በኢትዮጵያ በ12 ከተሞች አገልግሎቱን ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።
የአምስተኛው ትውልድ (5ጂ) የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት ደንበኞች ዘመኑን የሚመጥን ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
ዛሬ በጅማ የተጀመረው የአምስተኛው ትውልድ የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት በከተማዋና በአካባቢው የሚከናወኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ስራዎችን በተሻለ ደረጃ ለመከወን የሚያግዝ ነውም ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025