
ጅማ፤የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮ ቴሌኮም በጅማ ከተማ የአምስተኛውን ትውልድ የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት ዛሬ አስጀመረ።
በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩና የኩባንያው ከፍተኛ አመራር አባላት እንዲሁም የጅማ ከተማና የጅማ ዞን አመራሮችና የአገልግሎቱ ደንበኞች ተገኝተዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ፍሬህይወት ታምሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ኩባንያው አገልግሎት አሰጣጡን በማሻሻል ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን የማድረግ ጉዞ ላይ ነው።
የአምስተኛው ትውልድ ኔትወርክ አገልግሎት የዓለማችን ፈጣንና ቀልጣፋ የኔትወርክ አገልግሎት መሆኑን አንስተው አዲስ አበባን ጨምሮ በኢትዮጵያ በ12 ከተሞች አገልግሎቱን ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።
የአምስተኛው ትውልድ (5ጂ) የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት ደንበኞች ዘመኑን የሚመጥን ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
ዛሬ በጅማ የተጀመረው የአምስተኛው ትውልድ የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት በከተማዋና በአካባቢው የሚከናወኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ስራዎችን በተሻለ ደረጃ ለመከወን የሚያግዝ ነውም ብለዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026