አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበጎነት መንደር የተገነቡ የመኖሪያ ቤቶችን ለነዋሪዎች አስተላልፈዋል።
ዛሬ ለነዋሪዎች የተላለፉ ቤቶቹ በልደታ ክፍለ ከተማ በበጎነት መንደር የተገነቡ ሁለት ባለ ዘጠኝ ወለል የመኖሪያ ህንፃዎች ላይ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት የከተማዋን እድገት እና የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሁሉም ዜጋ በተባበረ ክንድ ከሰራ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ገልፀዋል።
ከተማ አስተዳደሩም የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በጀቱን በአግባቡ ተግባር ላይ በማዋልና ህዝቡን በንቃት በማሳተፍ የሚያከናውናቸው የልማት ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውንም ተናግረዋል።
በዛሬው ዕለትም በአስቸጋሪ የመኖሪያ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ አቅመ ደካማ ነዋሪዎች የዘመናዊ መኖሪያ ቤት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።
የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ አበባ እሸቴ እንዳሉት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ እና ምቹ ባልሆኑ መኖሪያዎች ውስጥ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች በዘመናዊ መኖሪያ ቤት መኖር እንዲችሉ ለማድረግ በሚሰሩ ተግባራት ባለሀብቶች ላደረጉት እገዛ ምስጋና አቅርበዋል።
የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አህመድ በበኩላቸው የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ለመቅረፍ በሚደረጉ ጥረቶች ግሩፑ የነቃ ተሳትፎ በማድረጉ ደስታ ይሰማናል ብለዋል።
የመኖሪያ ህንፃዎቹ ግንባታ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ጋራ በመተባበር የተከናወነ መሆኑም ተጠቅሷል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025