የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበጎነት መንደር የተገነቡ የመኖሪያ ቤቶችን ለነዋሪዎች አስተላለፉ</p>

Feb 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበጎነት መንደር የተገነቡ የመኖሪያ ቤቶችን ለነዋሪዎች አስተላልፈዋል።

ዛሬ ለነዋሪዎች የተላለፉ ቤቶቹ በልደታ ክፍለ ከተማ በበጎነት መንደር የተገነቡ ሁለት ባለ ዘጠኝ ወለል የመኖሪያ ህንፃዎች ላይ ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት የከተማዋን እድገት እና የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሁሉም ዜጋ በተባበረ ክንድ ከሰራ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ገልፀዋል።


ከተማ አስተዳደሩም የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በጀቱን በአግባቡ ተግባር ላይ በማዋልና ህዝቡን በንቃት በማሳተፍ የሚያከናውናቸው የልማት ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውንም ተናግረዋል።

በዛሬው ዕለትም በአስቸጋሪ የመኖሪያ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ አቅመ ደካማ ነዋሪዎች የዘመናዊ መኖሪያ ቤት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።


የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ አበባ እሸቴ እንዳሉት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ እና ምቹ ባልሆኑ መኖሪያዎች ውስጥ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች በዘመናዊ መኖሪያ ቤት መኖር እንዲችሉ ለማድረግ በሚሰሩ ተግባራት ባለሀብቶች ላደረጉት እገዛ ምስጋና አቅርበዋል።

የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አህመድ በበኩላቸው የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ለመቅረፍ በሚደረጉ ጥረቶች ግሩፑ የነቃ ተሳትፎ በማድረጉ ደስታ ይሰማናል ብለዋል።

የመኖሪያ ህንፃዎቹ ግንባታ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ጋራ በመተባበር የተከናወነ መሆኑም ተጠቅሷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025