
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበጎነት መንደር የተገነቡ የመኖሪያ ቤቶችን ለነዋሪዎች አስተላልፈዋል።
ዛሬ ለነዋሪዎች የተላለፉ ቤቶቹ በልደታ ክፍለ ከተማ በበጎነት መንደር የተገነቡ ሁለት ባለ ዘጠኝ ወለል የመኖሪያ ህንፃዎች ላይ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት የከተማዋን እድገት እና የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሁሉም ዜጋ በተባበረ ክንድ ከሰራ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ገልፀዋል።

ከተማ አስተዳደሩም የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በጀቱን በአግባቡ ተግባር ላይ በማዋልና ህዝቡን በንቃት በማሳተፍ የሚያከናውናቸው የልማት ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውንም ተናግረዋል።
በዛሬው ዕለትም በአስቸጋሪ የመኖሪያ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ አቅመ ደካማ ነዋሪዎች የዘመናዊ መኖሪያ ቤት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።

የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ አበባ እሸቴ እንዳሉት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ እና ምቹ ባልሆኑ መኖሪያዎች ውስጥ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች በዘመናዊ መኖሪያ ቤት መኖር እንዲችሉ ለማድረግ በሚሰሩ ተግባራት ባለሀብቶች ላደረጉት እገዛ ምስጋና አቅርበዋል።
የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አህመድ በበኩላቸው የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ለመቅረፍ በሚደረጉ ጥረቶች ግሩፑ የነቃ ተሳትፎ በማድረጉ ደስታ ይሰማናል ብለዋል።
የመኖሪያ ህንፃዎቹ ግንባታ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ጋራ በመተባበር የተከናወነ መሆኑም ተጠቅሷል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025