
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበጎነት መንደር የተገነቡ የመኖሪያ ቤቶችን ለነዋሪዎች አስተላልፈዋል።
ዛሬ ለነዋሪዎች የተላለፉ ቤቶቹ በልደታ ክፍለ ከተማ በበጎነት መንደር የተገነቡ ሁለት ባለ ዘጠኝ ወለል የመኖሪያ ህንፃዎች ላይ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት የከተማዋን እድገት እና የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሁሉም ዜጋ በተባበረ ክንድ ከሰራ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ገልፀዋል።

ከተማ አስተዳደሩም የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በጀቱን በአግባቡ ተግባር ላይ በማዋልና ህዝቡን በንቃት በማሳተፍ የሚያከናውናቸው የልማት ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውንም ተናግረዋል።
በዛሬው ዕለትም በአስቸጋሪ የመኖሪያ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ አቅመ ደካማ ነዋሪዎች የዘመናዊ መኖሪያ ቤት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።

የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ አበባ እሸቴ እንዳሉት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ እና ምቹ ባልሆኑ መኖሪያዎች ውስጥ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች በዘመናዊ መኖሪያ ቤት መኖር እንዲችሉ ለማድረግ በሚሰሩ ተግባራት ባለሀብቶች ላደረጉት እገዛ ምስጋና አቅርበዋል።
የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አህመድ በበኩላቸው የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ለመቅረፍ በሚደረጉ ጥረቶች ግሩፑ የነቃ ተሳትፎ በማድረጉ ደስታ ይሰማናል ብለዋል።
የመኖሪያ ህንፃዎቹ ግንባታ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ጋራ በመተባበር የተከናወነ መሆኑም ተጠቅሷል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026