
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፡- በሀረሪ ክልል ባለፉት ዓመታት በከተማ እና ገጠር ፍትሀዊ የሆነ የመሰረተ ልማት ተደራሽነት እንዲኖር የማስቻል ስራ መሰራቱ ተገልጿል።
በክልሉ በተለይም ወረዳን ከወረዳ ብሎም ገጠሩን ከከተማ ጋር የሚያገናኙ የአስፓልት እና የጠጠር መንገዶች ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውም ተመላክቷል።

ይህም አርሶ አደሩ ምርቱን በቀላሉ ለገበያ ማቅረብ እንዲችል እና የጉልበት የሃብትና የጊዜ ብክነትን ማስቀረት ማስቻሉም ተገልጿል።
የመንገድ ፕሮጀክቶቹ የአካባቢን ገፅታ ከመቀየር ባሻገር የአካባቢውን ኢኮኖሚ እንዲነቃቃም በማሳደግ ረገድ ጉልህ ፋይዳ እያበረከተ ይገኛል።
በዘንድሮው የበጀት አመትም ከ2 ቢሊየን ብር በላይ ለመንገድ ፕሮጀክት ተመድቦ እየተሰራ እንደሚገኝ ከክልሉ ኮሙኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025