አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፡- የደረሰኝ ልዩ መለያ ኮድ ወጥ፣ ዘመናዊና ፍትሐዊ የግብር አሰባስብ ስርዓት ለመዘርጋት እንደሚያስችል የገቢዎች ሚኒስቴር ገለፀ።
መንግስት ከሕገ ወጥ ደረሰኝ ሕትመትና ስርጭት ጋር ተያይዞ ያለውን ጉድለት የሚሸፍን ዘመናዊና ፍትሃዊ የሆነ የታክስ ስርዓት ለመገንባት በትኩረት እየሰራ ነው።
ገቢዎች ሚኒስቴርም ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ ማቅረቢያ ፎርም ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡
ልዩ መለያ ኮድ የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ነጋዴዎች ስራ ላይ እንዲያውሉትም የማድረግ ስራ ተግባራዊ ተደርጓል።
የገቢዎች ሚኒስቴር የመረጃና ቴክኖሎጂ ማዕከል ኃላፊ አቶ ክልሉ ታመነ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ዘመናዊና ቀልጣፋ የግብር አሰባሰብ ስርዓት ለመገንባት በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ተግባራዊ እየተደረገ ነው።
ሚኒስቴሩ ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ ማቅረቢያ ፎርምይፋ ማድረጉ እንደ ማሳያ ጠቅሰዋል።
ይህም ሕገ ወጥ የደረሰኝ ህትመትና ስርጭት በማስወገድ በዘርፉ አስተማማኝ የቁጥጥር ስራ ለማከናወን ያግዛል ብለዋል።
ከዚህም በተጨማሪም ልዩ መለያ ኮዱ ዘመናዊና እና ፍትሃዊ የሆነ የታክስ አሰባሰብ ስርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ታህሳስ ወር ላይ ደረሰኞቻቸውን ወስደው ወደ ስራ መግባታቸውንም አንስተዋል፡፡
አሁንም ተግባራዊ ያላደረጉ ነጋዴዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ወደ ስራ ያልገቡትን ለማስገባት ደረሰኝ የማሳተሚያ ጊዜውን እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲራዘም መደረጉን ጠቅሰዋል።
ነጋዴዎችም የተራዘመውን ጊዜ በመጠቀም ደረሰኞቻቸውን ወስደው ወደ ስራ መግባት እንደሚገባቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025