የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>የደረሰኝ ልዩ መለያ ኮድ ወጥ፣ ዘመናዊና ፍትሐዊ የግብር አሰባስብ ስርዓት ለመዘርጋት ያስችላል- ገቢዎች ሚኒስቴር</p>

Feb 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፡- የደረሰኝ ልዩ መለያ ኮድ ወጥ፣ ዘመናዊና ፍትሐዊ የግብር አሰባስብ ስርዓት ለመዘርጋት እንደሚያስችል የገቢዎች ሚኒስቴር ገለፀ።

መንግስት ከሕገ ወጥ ደረሰኝ ሕትመትና ስርጭት ጋር ተያይዞ ያለውን ጉድለት የሚሸፍን ዘመናዊና ፍትሃዊ የሆነ የታክስ ስርዓት ለመገንባት በትኩረት እየሰራ ነው።

ገቢዎች ሚኒስቴርም ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ ማቅረቢያ ፎርም ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡

ልዩ መለያ ኮድ የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ነጋዴዎች ስራ ላይ እንዲያውሉትም የማድረግ ስራ ተግባራዊ ተደርጓል።

የገቢዎች ሚኒስቴር የመረጃና ቴክኖሎጂ ማዕከል ኃላፊ አቶ ክልሉ ታመነ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ዘመናዊና ቀልጣፋ የግብር አሰባሰብ ስርዓት ለመገንባት በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ተግባራዊ እየተደረገ ነው።

ሚኒስቴሩ ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ ማቅረቢያ ፎርምይፋ ማድረጉ እንደ ማሳያ ጠቅሰዋል።

ይህም ሕገ ወጥ የደረሰኝ ህትመትና ስርጭት በማስወገድ በዘርፉ አስተማማኝ የቁጥጥር ስራ ለማከናወን ያግዛል ብለዋል።

ከዚህም በተጨማሪም ልዩ መለያ ኮዱ ዘመናዊና እና ፍትሃዊ የሆነ የታክስ አሰባሰብ ስርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ታህሳስ ወር ላይ ደረሰኞቻቸውን ወስደው ወደ ስራ መግባታቸውንም አንስተዋል፡፡

አሁንም ተግባራዊ ያላደረጉ ነጋዴዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ወደ ስራ ያልገቡትን ለማስገባት ደረሰኝ የማሳተሚያ ጊዜውን እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲራዘም መደረጉን ጠቅሰዋል።

ነጋዴዎችም የተራዘመውን ጊዜ በመጠቀም ደረሰኞቻቸውን ወስደው ወደ ስራ መግባት እንደሚገባቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025