
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፡- የደረሰኝ ልዩ መለያ ኮድ ወጥ፣ ዘመናዊና ፍትሐዊ የግብር አሰባስብ ስርዓት ለመዘርጋት እንደሚያስችል የገቢዎች ሚኒስቴር ገለፀ።
መንግስት ከሕገ ወጥ ደረሰኝ ሕትመትና ስርጭት ጋር ተያይዞ ያለውን ጉድለት የሚሸፍን ዘመናዊና ፍትሃዊ የሆነ የታክስ ስርዓት ለመገንባት በትኩረት እየሰራ ነው።
ገቢዎች ሚኒስቴርም ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ ማቅረቢያ ፎርም ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡
ልዩ መለያ ኮድ የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ነጋዴዎች ስራ ላይ እንዲያውሉትም የማድረግ ስራ ተግባራዊ ተደርጓል።
የገቢዎች ሚኒስቴር የመረጃና ቴክኖሎጂ ማዕከል ኃላፊ አቶ ክልሉ ታመነ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ዘመናዊና ቀልጣፋ የግብር አሰባሰብ ስርዓት ለመገንባት በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ተግባራዊ እየተደረገ ነው።
ሚኒስቴሩ ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ ማቅረቢያ ፎርምይፋ ማድረጉ እንደ ማሳያ ጠቅሰዋል።
ይህም ሕገ ወጥ የደረሰኝ ህትመትና ስርጭት በማስወገድ በዘርፉ አስተማማኝ የቁጥጥር ስራ ለማከናወን ያግዛል ብለዋል።
ከዚህም በተጨማሪም ልዩ መለያ ኮዱ ዘመናዊና እና ፍትሃዊ የሆነ የታክስ አሰባሰብ ስርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ታህሳስ ወር ላይ ደረሰኞቻቸውን ወስደው ወደ ስራ መግባታቸውንም አንስተዋል፡፡
አሁንም ተግባራዊ ያላደረጉ ነጋዴዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ወደ ስራ ያልገቡትን ለማስገባት ደረሰኝ የማሳተሚያ ጊዜውን እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲራዘም መደረጉን ጠቅሰዋል።
ነጋዴዎችም የተራዘመውን ጊዜ በመጠቀም ደረሰኞቻቸውን ወስደው ወደ ስራ መግባት እንደሚገባቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026