
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፡- የደረሰኝ ልዩ መለያ ኮድ ወጥ፣ ዘመናዊና ፍትሐዊ የግብር አሰባስብ ስርዓት ለመዘርጋት እንደሚያስችል የገቢዎች ሚኒስቴር ገለፀ።
መንግስት ከሕገ ወጥ ደረሰኝ ሕትመትና ስርጭት ጋር ተያይዞ ያለውን ጉድለት የሚሸፍን ዘመናዊና ፍትሃዊ የሆነ የታክስ ስርዓት ለመገንባት በትኩረት እየሰራ ነው።
ገቢዎች ሚኒስቴርም ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ ማቅረቢያ ፎርም ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡
ልዩ መለያ ኮድ የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ነጋዴዎች ስራ ላይ እንዲያውሉትም የማድረግ ስራ ተግባራዊ ተደርጓል።
የገቢዎች ሚኒስቴር የመረጃና ቴክኖሎጂ ማዕከል ኃላፊ አቶ ክልሉ ታመነ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ዘመናዊና ቀልጣፋ የግብር አሰባሰብ ስርዓት ለመገንባት በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ተግባራዊ እየተደረገ ነው።
ሚኒስቴሩ ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ ማቅረቢያ ፎርምይፋ ማድረጉ እንደ ማሳያ ጠቅሰዋል።
ይህም ሕገ ወጥ የደረሰኝ ህትመትና ስርጭት በማስወገድ በዘርፉ አስተማማኝ የቁጥጥር ስራ ለማከናወን ያግዛል ብለዋል።
ከዚህም በተጨማሪም ልዩ መለያ ኮዱ ዘመናዊና እና ፍትሃዊ የሆነ የታክስ አሰባሰብ ስርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ታህሳስ ወር ላይ ደረሰኞቻቸውን ወስደው ወደ ስራ መግባታቸውንም አንስተዋል፡፡
አሁንም ተግባራዊ ያላደረጉ ነጋዴዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ወደ ስራ ያልገቡትን ለማስገባት ደረሰኝ የማሳተሚያ ጊዜውን እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲራዘም መደረጉን ጠቅሰዋል።
ነጋዴዎችም የተራዘመውን ጊዜ በመጠቀም ደረሰኞቻቸውን ወስደው ወደ ስራ መግባት እንደሚገባቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025