ገንዳ ውሃ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፡- በመተማ ከተማ የተገነባው የእንስሳት ማቆያን/ኳራንታይን/ ፈጥኖ ወደ ስራ ለማስገባት ጥረት እየተደረገ መሆኑ የምዕራብ ጎንደር ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ገለጸ።
የእንስሳት ኮንትሮባንድ ንግድ መከላከል ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ዛሬ በገንዳ ውሃ ከተማ ተካሂዷል።
የምዕራብ ጎንደር ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ጌትነት በሊሁን በመድረኩ ላይ እንደተናገሩት ዞኑ ጠረፋማ በመሆኑ በአብዛኛው ለኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድ የተጋለጠ ነው።
በአካባቢው ያለውን የእንስሳት እምቅ ሃብት በህገ ወጥ ነጋዴዎች አማካኝነት እየባከነ መሆኑን ተናግረዋል።
ችግሩን ለማቃለል በ30 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን የእንስሳት ማቆያ ወደ ስራ ለማስገባት ከባለድርሻ ተቋማት ጋር የተቀናጀ ጥረት እየደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃለፊ አቶ አንዳርጌ ጌጡ እንዳሉት፤ ዞኑ ለወጭ ንግድ ከሚመረተው ሰሊጥ፣ አኩሪ አተር፣ ጥጥና ሌሎች ምርቶች ባሻገር ሰፊ የእንስሳት ሀብት ባለቤት ነው።
በፀጋው ልክ በመስራት ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚያስፈልግ ጠቁመው፤ ለዚህም ህገወጥ የቁም እንስሳት ንግድን ለመከላከል የሚያግዝ ማቆያው(ኳራንታይኑ) ስራ እንዲጀምር ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማቆያው (ኳራንታይኑ) ስራ አስኪያጅ ፀጋዬ ብርቱዓለም(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ማቆያው(ኳራንታይኑ) የተሟላ የሰው ኃይልና ግንባታ ያለው በመሆኑ ወደ ስራ መግባት ለሚፈልጉ ላኪዎች የፈቃድ ማረጋገጫ መስጠት እንደሚቻል አብራርተዋል።
የመተማ ዮሃንስ ጉምሩክ ቅርንጫፍ አስተባባሪ አቶ አማረ ብርሌ በበኩላቸው፤ የቁም እንስሳት ኮንትሮባንድን ለመከላከል እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ባለፉት ሁለት ወራት ብቻ 318 የቁም እንስሳት ወደ ውጭ ለማሻገር ሲሞከር መያዙን ጠቅሰው፤ ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር እንቅስቃሴውን ማስቆም ይቻላል ብለዋል።
በውይይት መድረኩ የዞኑ፣ የከተማ አስተዳደር አመራር አባላት፣ የጉምሩክ ስራ ኃላፊዎች፣ የፀጥታ አካላት እና ሌሎች ባለድርሻዎች ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025