
ገንዳ ውሃ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፡- በመተማ ከተማ የተገነባው የእንስሳት ማቆያን/ኳራንታይን/ ፈጥኖ ወደ ስራ ለማስገባት ጥረት እየተደረገ መሆኑ የምዕራብ ጎንደር ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ገለጸ።
የእንስሳት ኮንትሮባንድ ንግድ መከላከል ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ዛሬ በገንዳ ውሃ ከተማ ተካሂዷል።
የምዕራብ ጎንደር ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ጌትነት በሊሁን በመድረኩ ላይ እንደተናገሩት ዞኑ ጠረፋማ በመሆኑ በአብዛኛው ለኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድ የተጋለጠ ነው።
በአካባቢው ያለውን የእንስሳት እምቅ ሃብት በህገ ወጥ ነጋዴዎች አማካኝነት እየባከነ መሆኑን ተናግረዋል።
ችግሩን ለማቃለል በ30 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን የእንስሳት ማቆያ ወደ ስራ ለማስገባት ከባለድርሻ ተቋማት ጋር የተቀናጀ ጥረት እየደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃለፊ አቶ አንዳርጌ ጌጡ እንዳሉት፤ ዞኑ ለወጭ ንግድ ከሚመረተው ሰሊጥ፣ አኩሪ አተር፣ ጥጥና ሌሎች ምርቶች ባሻገር ሰፊ የእንስሳት ሀብት ባለቤት ነው።
በፀጋው ልክ በመስራት ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚያስፈልግ ጠቁመው፤ ለዚህም ህገወጥ የቁም እንስሳት ንግድን ለመከላከል የሚያግዝ ማቆያው(ኳራንታይኑ) ስራ እንዲጀምር ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማቆያው (ኳራንታይኑ) ስራ አስኪያጅ ፀጋዬ ብርቱዓለም(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ማቆያው(ኳራንታይኑ) የተሟላ የሰው ኃይልና ግንባታ ያለው በመሆኑ ወደ ስራ መግባት ለሚፈልጉ ላኪዎች የፈቃድ ማረጋገጫ መስጠት እንደሚቻል አብራርተዋል።
የመተማ ዮሃንስ ጉምሩክ ቅርንጫፍ አስተባባሪ አቶ አማረ ብርሌ በበኩላቸው፤ የቁም እንስሳት ኮንትሮባንድን ለመከላከል እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ባለፉት ሁለት ወራት ብቻ 318 የቁም እንስሳት ወደ ውጭ ለማሻገር ሲሞከር መያዙን ጠቅሰው፤ ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር እንቅስቃሴውን ማስቆም ይቻላል ብለዋል።
በውይይት መድረኩ የዞኑ፣ የከተማ አስተዳደር አመራር አባላት፣ የጉምሩክ ስራ ኃላፊዎች፣ የፀጥታ አካላት እና ሌሎች ባለድርሻዎች ተሳትፈዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025