
ጅማ፣ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ ምሁራን ዘላቂ ሀገራዊ ሰላምና ብሔራዊ ጥቅም የሚበጁ የስትራቴጂና ፖሊሲ ግብዓት ምክረ ሀሳቦችን እንዲያቀርቡ ተጠየቀ።
“አገራዊ ጥቅሞቻችንና ቀጣናዊ ትስስር ለህዝቦች ሚዛናዊ ተጠቃሚነት” በሚል መሪ ሃሳብ በሰላም ሚኒስቴርና ጅማ ዩኒቨርሲቲ ትብብር የተዘጋጀ የምሁራን የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት (ዶ/ር) ጀማል አባ ፊጣ ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሚሻ ጠቅሰዋል።
ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማረጋገጥም የምሁራን ተሳትፎ የላቀ ነው ብለዋል።
የመነሻ ፅሁፍ ያቀረቡት በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካል ሳይንስ ምሁር ኢድሪስ የባ (ዶ/ር) የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዎች ከብሔራዊ ጥቅምና ከቀጣናዊ ትስስር ጋር መቃኘት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
ቀጣናዊ ትስስርን ለፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል፣ ማህበራዊ ፍትህና ኢኮኖሚያዊ እመርታ ካለው ፋይዳ አኳያ ማጎልበት ይገባል ብለዋል።
በዚህም ምሁራን ጥናትና ምርምር በማካሄድ የስትራቴጂና ፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ ምክረ ሀሳቦችን በማቅረብ ሚናቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
በሰላም ሚኒስቴር የሀገር ግንባታ መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ሀለፎም አባይ በበኩላቸው፤ ሚኒስቴሩ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር ምሁራንን ለሀገርና ህዝብ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥሩ ሀሳቦችን እንዲያፈልቁ ምቹ መደላድል አመቻችቷል ብለዋል።

የውይይት መደረኩ የሀገር ብሔራዊ ጥቅም ከቀጣናዊ ትስስር አኳያ ያለውን ሁሉን አቀፍ ፋይዳ ለመቃኘት ያለመ ስለመሆኑ ጠቅሰዋል።
በሀገሪቱ ሰላምን በማስፈን ልማትን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ቀጣናዊና አለም አቀፋዊ ግንኙነት ለማጎልበት የፖሊሲ እና የስትራቴጂ አቅጣጫዎችን ለመከተል ያግዛል ነው ያሉት።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026