
ጅማ፣ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ ምሁራን ዘላቂ ሀገራዊ ሰላምና ብሔራዊ ጥቅም የሚበጁ የስትራቴጂና ፖሊሲ ግብዓት ምክረ ሀሳቦችን እንዲያቀርቡ ተጠየቀ።
“አገራዊ ጥቅሞቻችንና ቀጣናዊ ትስስር ለህዝቦች ሚዛናዊ ተጠቃሚነት” በሚል መሪ ሃሳብ በሰላም ሚኒስቴርና ጅማ ዩኒቨርሲቲ ትብብር የተዘጋጀ የምሁራን የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት (ዶ/ር) ጀማል አባ ፊጣ ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሚሻ ጠቅሰዋል።
ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማረጋገጥም የምሁራን ተሳትፎ የላቀ ነው ብለዋል።
የመነሻ ፅሁፍ ያቀረቡት በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካል ሳይንስ ምሁር ኢድሪስ የባ (ዶ/ር) የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዎች ከብሔራዊ ጥቅምና ከቀጣናዊ ትስስር ጋር መቃኘት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
ቀጣናዊ ትስስርን ለፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል፣ ማህበራዊ ፍትህና ኢኮኖሚያዊ እመርታ ካለው ፋይዳ አኳያ ማጎልበት ይገባል ብለዋል።
በዚህም ምሁራን ጥናትና ምርምር በማካሄድ የስትራቴጂና ፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ ምክረ ሀሳቦችን በማቅረብ ሚናቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
በሰላም ሚኒስቴር የሀገር ግንባታ መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ሀለፎም አባይ በበኩላቸው፤ ሚኒስቴሩ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር ምሁራንን ለሀገርና ህዝብ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥሩ ሀሳቦችን እንዲያፈልቁ ምቹ መደላድል አመቻችቷል ብለዋል።

የውይይት መደረኩ የሀገር ብሔራዊ ጥቅም ከቀጣናዊ ትስስር አኳያ ያለውን ሁሉን አቀፍ ፋይዳ ለመቃኘት ያለመ ስለመሆኑ ጠቅሰዋል።
በሀገሪቱ ሰላምን በማስፈን ልማትን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ቀጣናዊና አለም አቀፋዊ ግንኙነት ለማጎልበት የፖሊሲ እና የስትራቴጂ አቅጣጫዎችን ለመከተል ያግዛል ነው ያሉት።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025