የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቁ ምክረ ሀሳቦች ከምሁራን ይጠበቃሉ</p>

Feb 20, 2025

IDOPRESS

ጅማ፣ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ ምሁራን ዘላቂ ሀገራዊ ሰላምና ብሔራዊ ጥቅም የሚበጁ የስትራቴጂና ፖሊሲ ግብዓት ምክረ ሀሳቦችን እንዲያቀርቡ ተጠየቀ።

“አገራዊ ጥቅሞቻችንና ቀጣናዊ ትስስር ለህዝቦች ሚዛናዊ ተጠቃሚነት” በሚል መሪ ሃሳብ በሰላም ሚኒስቴርና ጅማ ዩኒቨርሲቲ ትብብር የተዘጋጀ የምሁራን የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት (ዶ/ር) ጀማል አባ ፊጣ ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሚሻ ጠቅሰዋል።

ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማረጋገጥም የምሁራን ተሳትፎ የላቀ ነው ብለዋል።

የመነሻ ፅሁፍ ያቀረቡት በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካል ሳይንስ ምሁር ኢድሪስ የባ (ዶ/ር) የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዎች ከብሔራዊ ጥቅምና ከቀጣናዊ ትስስር ጋር መቃኘት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

ቀጣናዊ ትስስርን ለፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል፣ ማህበራዊ ፍትህና ኢኮኖሚያዊ እመርታ ካለው ፋይዳ አኳያ ማጎልበት ይገባል ብለዋል።

በዚህም ምሁራን ጥናትና ምርምር በማካሄድ የስትራቴጂና ፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ ምክረ ሀሳቦችን በማቅረብ ሚናቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

በሰላም ሚኒስቴር የሀገር ግንባታ መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ሀለፎም አባይ በበኩላቸው፤ ሚኒስቴሩ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር ምሁራንን ለሀገርና ህዝብ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥሩ ሀሳቦችን እንዲያፈልቁ ምቹ መደላድል አመቻችቷል ብለዋል።

የውይይት መደረኩ የሀገር ብሔራዊ ጥቅም ከቀጣናዊ ትስስር አኳያ ያለውን ሁሉን አቀፍ ፋይዳ ለመቃኘት ያለመ ስለመሆኑ ጠቅሰዋል።

በሀገሪቱ ሰላምን በማስፈን ልማትን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ቀጣናዊና አለም አቀፋዊ ግንኙነት ለማጎልበት የፖሊሲ እና የስትራቴጂ አቅጣጫዎችን ለመከተል ያግዛል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026