የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>ጉባዔውን በተቀናጀ መልኩ ለማስተናገድ ዘርፈ ብዙ ዝግጅቶች እየተደረጉ ነው</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- 2ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ ስርዓት ጉባዔን በተቀናጀ መልኩ ለማስተናገድ ዘርፈ ብዙ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ።


በመጪው ሐምሌ ወር 2017ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚካሄደውን 2ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ ስርዓት ጉባዔን በስኬት ለማስተናገድ በተጀመሩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል።

በውይይቱ ላይ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ጉባዔውን በተቀናጀ መልኩ ለማስተናገድ ዘርፈ ብዙ ዝግጅቶች እየተደረጉ ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ በምግብ ራስን ለመቻል እየተደረጉ ያሉ ተግባር ተኮር እና ለውጥ ያመጡ ሥራዎችን በተመለከተም ገለፃ አድርገዋል።


የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ በርካታ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ኮንፍረንሶችን በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን አስታውሰዋል።

ሐምሌ ወር በአዲስ አበባ ለሚካሄደው ጉባኤም ኢትዮጵያ ያላትን አቅም በመጠቀም የተሟላ ዝግጅት እንደምታደርግ መናገራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል።


የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልዑካን ቡድን መሪ እስጢፋኖስ ፎሽው(ዶር) ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በመንግሥት እየተከናወነ ያሉ የልማት እንቅስቃሴዎችን በማድነቅ ጉባዔውን በተሳካ ሁኔታ እንደምታስተናግድ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።

በዚህ የጉባዔ ቅድመ ዝግጅት የኮሜቴ ውይይት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተቋማት እና በጣሊያን የኢትዮጵያ ኤምባሲ፣ በኒውዮርክ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ጽህፈት ቤት አምባሳደሮች እና ከፍተኛ ባለሙያዎች መሳተፋቸውም ተጠቅሷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025