
አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- 2ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ ስርዓት ጉባዔን በተቀናጀ መልኩ ለማስተናገድ ዘርፈ ብዙ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ።

በመጪው ሐምሌ ወር 2017ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚካሄደውን 2ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ ስርዓት ጉባዔን በስኬት ለማስተናገድ በተጀመሩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል።
በውይይቱ ላይ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ጉባዔውን በተቀናጀ መልኩ ለማስተናገድ ዘርፈ ብዙ ዝግጅቶች እየተደረጉ ነው ብለዋል።
በኢትዮጵያ በምግብ ራስን ለመቻል እየተደረጉ ያሉ ተግባር ተኮር እና ለውጥ ያመጡ ሥራዎችን በተመለከተም ገለፃ አድርገዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ በርካታ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ኮንፍረንሶችን በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን አስታውሰዋል።
ሐምሌ ወር በአዲስ አበባ ለሚካሄደው ጉባኤም ኢትዮጵያ ያላትን አቅም በመጠቀም የተሟላ ዝግጅት እንደምታደርግ መናገራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልዑካን ቡድን መሪ እስጢፋኖስ ፎሽው(ዶር) ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በመንግሥት እየተከናወነ ያሉ የልማት እንቅስቃሴዎችን በማድነቅ ጉባዔውን በተሳካ ሁኔታ እንደምታስተናግድ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።
በዚህ የጉባዔ ቅድመ ዝግጅት የኮሜቴ ውይይት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተቋማት እና በጣሊያን የኢትዮጵያ ኤምባሲ፣ በኒውዮርክ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ጽህፈት ቤት አምባሳደሮች እና ከፍተኛ ባለሙያዎች መሳተፋቸውም ተጠቅሷል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025