
አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- 2ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ ስርዓት ጉባዔን በተቀናጀ መልኩ ለማስተናገድ ዘርፈ ብዙ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ።

በመጪው ሐምሌ ወር 2017ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚካሄደውን 2ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ ስርዓት ጉባዔን በስኬት ለማስተናገድ በተጀመሩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል።
በውይይቱ ላይ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ጉባዔውን በተቀናጀ መልኩ ለማስተናገድ ዘርፈ ብዙ ዝግጅቶች እየተደረጉ ነው ብለዋል።
በኢትዮጵያ በምግብ ራስን ለመቻል እየተደረጉ ያሉ ተግባር ተኮር እና ለውጥ ያመጡ ሥራዎችን በተመለከተም ገለፃ አድርገዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ በርካታ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ኮንፍረንሶችን በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን አስታውሰዋል።
ሐምሌ ወር በአዲስ አበባ ለሚካሄደው ጉባኤም ኢትዮጵያ ያላትን አቅም በመጠቀም የተሟላ ዝግጅት እንደምታደርግ መናገራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልዑካን ቡድን መሪ እስጢፋኖስ ፎሽው(ዶር) ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በመንግሥት እየተከናወነ ያሉ የልማት እንቅስቃሴዎችን በማድነቅ ጉባዔውን በተሳካ ሁኔታ እንደምታስተናግድ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።
በዚህ የጉባዔ ቅድመ ዝግጅት የኮሜቴ ውይይት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተቋማት እና በጣሊያን የኢትዮጵያ ኤምባሲ፣ በኒውዮርክ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ጽህፈት ቤት አምባሳደሮች እና ከፍተኛ ባለሙያዎች መሳተፋቸውም ተጠቅሷል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026