ደሴ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮ ቴሌኮም በደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች የአምስተኛው ትውልድ(5ጂ) ኔትወርክ አገልግሎት አስጀመረ።
በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የተገኙት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ፤ የአምስተኛው ትውልድ ኔትወርክ ከፍትኛ ፍጥነት ያለው የኢንተርኔት አገልግሎትን እውን የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም ኢትዮ ቴሌኮም በሁሉም አካባቢዎች የአምስተኛው ትውልድ(5ጂ) ኔትወርክ እንዲስፋፋ አበክሮ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
የአገልግሎቱ መጀመር የኔትወርክ አቅምን ከመጨመር ባለፈ አዳዲስ የዲጂታል እና የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ ለኦንላይን ትምህርት፣ ለጀማሪ የንግድ ተቋማት፣ ለስራ እድል ፈጠራ፣ የዲጂታል ክፍተትን ለማጥበብ፣ የስማርት ስልክ አቅርቦት ለማሳደግ አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራልም ብለዋል።
በጤና፣ በግብርና፣ በትምህርት፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በማዕድን፣ በትራንስፖርት፣ በቱሪዝምና ለሌሎች ዘርፎች አገልግሎቱ የላቀ ፋይዳ ያለው መሆኑንም አብራርተዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም ከቀናት በፊት በተመሳሳይ በጅማ ከተማ የ5ጂ ኔትወርክ አገልግሎት ይፋ ማድረጉ ይታወቃል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025