
ደሴ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮ ቴሌኮም በደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች የአምስተኛው ትውልድ(5ጂ) ኔትወርክ አገልግሎት አስጀመረ።
በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የተገኙት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ፤ የአምስተኛው ትውልድ ኔትወርክ ከፍትኛ ፍጥነት ያለው የኢንተርኔት አገልግሎትን እውን የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም ኢትዮ ቴሌኮም በሁሉም አካባቢዎች የአምስተኛው ትውልድ(5ጂ) ኔትወርክ እንዲስፋፋ አበክሮ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
የአገልግሎቱ መጀመር የኔትወርክ አቅምን ከመጨመር ባለፈ አዳዲስ የዲጂታል እና የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ ለኦንላይን ትምህርት፣ ለጀማሪ የንግድ ተቋማት፣ ለስራ እድል ፈጠራ፣ የዲጂታል ክፍተትን ለማጥበብ፣ የስማርት ስልክ አቅርቦት ለማሳደግ አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራልም ብለዋል።
በጤና፣ በግብርና፣ በትምህርት፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በማዕድን፣ በትራንስፖርት፣ በቱሪዝምና ለሌሎች ዘርፎች አገልግሎቱ የላቀ ፋይዳ ያለው መሆኑንም አብራርተዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም ከቀናት በፊት በተመሳሳይ በጅማ ከተማ የ5ጂ ኔትወርክ አገልግሎት ይፋ ማድረጉ ይታወቃል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026