
ደሴ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮ ቴሌኮም በደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች የአምስተኛው ትውልድ(5ጂ) ኔትወርክ አገልግሎት አስጀመረ።
በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የተገኙት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ፤ የአምስተኛው ትውልድ ኔትወርክ ከፍትኛ ፍጥነት ያለው የኢንተርኔት አገልግሎትን እውን የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም ኢትዮ ቴሌኮም በሁሉም አካባቢዎች የአምስተኛው ትውልድ(5ጂ) ኔትወርክ እንዲስፋፋ አበክሮ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
የአገልግሎቱ መጀመር የኔትወርክ አቅምን ከመጨመር ባለፈ አዳዲስ የዲጂታል እና የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ ለኦንላይን ትምህርት፣ ለጀማሪ የንግድ ተቋማት፣ ለስራ እድል ፈጠራ፣ የዲጂታል ክፍተትን ለማጥበብ፣ የስማርት ስልክ አቅርቦት ለማሳደግ አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራልም ብለዋል።
በጤና፣ በግብርና፣ በትምህርት፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በማዕድን፣ በትራንስፖርት፣ በቱሪዝምና ለሌሎች ዘርፎች አገልግሎቱ የላቀ ፋይዳ ያለው መሆኑንም አብራርተዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም ከቀናት በፊት በተመሳሳይ በጅማ ከተማ የ5ጂ ኔትወርክ አገልግሎት ይፋ ማድረጉ ይታወቃል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025