
ድሬዳዋ፣ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ አስተዳደር በልማታዊ ሴፍቲኔት መርሐ ግብር የታቀፉ ዜጎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች ውጤት እያስገኙ መሆኑን የስራና ከህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ ገለጹ።
በሚኒስትር ዴኤታው አቶ ሰለሞን ሶካ የተመራ የፌደራልና የአስተዳደሩ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች ቡድን በድሬዳዋ ዜጎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን የመስክ ግምገማ አድርጓል።
ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ወቅት ህብረተሰቡን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር የተለያዩ መርሐ ግብሮችን ገቢራዊ እየተደረጉ ስለመሆኑ ጠቅሰው፤ ልማታዊ ሴፍቲኔትን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በድሬዳዋ አስተዳደር በዚሁ መርሐ ግብሩ የታቀፉ የማህበረሰብ ክፍሎች በተደረገላቸው ድጋፍ ወደ ምርታማነት እየተሸጋገሩ መሆኑን ገልጸዋል።
የመስክ ምልከታው በድሬዳዋ አስተዳደር ሲጠናቀቅ በቀጣይ በሐረሪ ክልል እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025