
ድሬዳዋ፣ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ አስተዳደር በልማታዊ ሴፍቲኔት መርሐ ግብር የታቀፉ ዜጎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች ውጤት እያስገኙ መሆኑን የስራና ከህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ ገለጹ።
በሚኒስትር ዴኤታው አቶ ሰለሞን ሶካ የተመራ የፌደራልና የአስተዳደሩ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች ቡድን በድሬዳዋ ዜጎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን የመስክ ግምገማ አድርጓል።
ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ወቅት ህብረተሰቡን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር የተለያዩ መርሐ ግብሮችን ገቢራዊ እየተደረጉ ስለመሆኑ ጠቅሰው፤ ልማታዊ ሴፍቲኔትን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በድሬዳዋ አስተዳደር በዚሁ መርሐ ግብሩ የታቀፉ የማህበረሰብ ክፍሎች በተደረገላቸው ድጋፍ ወደ ምርታማነት እየተሸጋገሩ መሆኑን ገልጸዋል።
የመስክ ምልከታው በድሬዳዋ አስተዳደር ሲጠናቀቅ በቀጣይ በሐረሪ ክልል እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026