
አሶሳ ፤ የካቲት 17/2017(ኢዜአ):- ኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎችን በልማት የማስተሳሰሩ ስራ እንደሚጠናከር የሁለቱ ክልሎች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ተናገሩ።
በኦሮሚያ ክልል መንግስት ድጋፍ በ225 ሚሊዮን ብር ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ዞን ኡራ ወረዳ የተገነባው የባሮ ኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመርቋል።

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ በወቅቱ እንደተናገሩት የሁለቱን ክልል ህዝቦች የጋራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወኑ ያሉ የልማትና የትብብር ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ።
ሁለቱ ክልሎች ከዚህ በተሻለ የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መስኮች ያላቸው ትስስሮች እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
''በአንድነት እና በመተጋገዝ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው'' ያሉት አቶ ሽመልስ፤ ለዚህም ማሳያው የሁለቱ ክልሎች የጋራ ልማት ነው ብለዋል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በበኩላቸው የሁለቱ ህዝቦችን የቆየ ወዳጅነት በልማት ስራዎች ለማስቀጠል የተጀመረው ስራ ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል።
በሁለቱ ክልሎች መካከል ያለውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግም የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል።
''በህዝቦች መካከል ፀንቶ የቆየውን አብሮነት ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር ለሌሎችም ተሞክሮ ለማድረግ እንሰራለን፤ ይህም ይጠናከራል'' ብለዋል።
''ትምህርት ቤቱ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት አጋዥ ይሆናል'' ያሉት ደግሞ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ተመስገን ዲሳሳ (ዶ/ር) ናቸው።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026