አሶሳ ፤ የካቲት 17/2017(ኢዜአ):- ኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎችን በልማት የማስተሳሰሩ ስራ እንደሚጠናከር የሁለቱ ክልሎች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ተናገሩ።
በኦሮሚያ ክልል መንግስት ድጋፍ በ225 ሚሊዮን ብር ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ዞን ኡራ ወረዳ የተገነባው የባሮ ኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመርቋል።
የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ በወቅቱ እንደተናገሩት የሁለቱን ክልል ህዝቦች የጋራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወኑ ያሉ የልማትና የትብብር ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ።
ሁለቱ ክልሎች ከዚህ በተሻለ የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መስኮች ያላቸው ትስስሮች እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
''በአንድነት እና በመተጋገዝ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው'' ያሉት አቶ ሽመልስ፤ ለዚህም ማሳያው የሁለቱ ክልሎች የጋራ ልማት ነው ብለዋል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በበኩላቸው የሁለቱ ህዝቦችን የቆየ ወዳጅነት በልማት ስራዎች ለማስቀጠል የተጀመረው ስራ ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል።
በሁለቱ ክልሎች መካከል ያለውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግም የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል።
''በህዝቦች መካከል ፀንቶ የቆየውን አብሮነት ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር ለሌሎችም ተሞክሮ ለማድረግ እንሰራለን፤ ይህም ይጠናከራል'' ብለዋል።
''ትምህርት ቤቱ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት አጋዥ ይሆናል'' ያሉት ደግሞ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ተመስገን ዲሳሳ (ዶ/ር) ናቸው።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025