
አሶሳ ፤ የካቲት 17/2017(ኢዜአ):- ኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎችን በልማት የማስተሳሰሩ ስራ እንደሚጠናከር የሁለቱ ክልሎች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ተናገሩ።
በኦሮሚያ ክልል መንግስት ድጋፍ በ225 ሚሊዮን ብር ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ዞን ኡራ ወረዳ የተገነባው የባሮ ኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመርቋል።

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ በወቅቱ እንደተናገሩት የሁለቱን ክልል ህዝቦች የጋራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወኑ ያሉ የልማትና የትብብር ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ።
ሁለቱ ክልሎች ከዚህ በተሻለ የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መስኮች ያላቸው ትስስሮች እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
''በአንድነት እና በመተጋገዝ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው'' ያሉት አቶ ሽመልስ፤ ለዚህም ማሳያው የሁለቱ ክልሎች የጋራ ልማት ነው ብለዋል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በበኩላቸው የሁለቱ ህዝቦችን የቆየ ወዳጅነት በልማት ስራዎች ለማስቀጠል የተጀመረው ስራ ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል።
በሁለቱ ክልሎች መካከል ያለውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግም የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል።
''በህዝቦች መካከል ፀንቶ የቆየውን አብሮነት ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር ለሌሎችም ተሞክሮ ለማድረግ እንሰራለን፤ ይህም ይጠናከራል'' ብለዋል።
''ትምህርት ቤቱ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት አጋዥ ይሆናል'' ያሉት ደግሞ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ተመስገን ዲሳሳ (ዶ/ር) ናቸው።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025